እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በርባን ፡ በእውነቱ ፡ ነፍሰ ፡ ገዳይ ፡ ነበርን ፡ ወይስ ፡ ታጋይና ፡ ጀግና ?

በርባን ፡ በእውነቱ ፡ ነፍሰ ፡ ገዳይ ፡ ነበርን ፡ ወይስ ፡ ታጋይና ፡ ጀግና ?

የበርባንን ፡ ታሪክ ፡ በምናይበት ፡ ጊዜ ፡ አራቱም ፡ ወንጌላውያን ፡ በርባን ፡ ስለተባለ ፡ ሰው ፡ ይተርካሉ ፡፡ ይህም ፡ ኢየሱስ ፡ ለፍርድ ፡ በቀረበ ፡ ጊዜ ፡ አይሁዳውያን ‹‹ኢየሱስ ፡ ይሰቀል ፡ በርባን ፡ ግን ፡ ይፈታ ›› እያሉ ፡ ሲጮሁ ፡ እንደነበረና ፡ በርባንም ፡ ‹‹የሕዝብ ፡ ዐመፅ ፡ በማነሣሣት ፡ በነፍስ ፡ ግድያ ፡ የታሰረ ›› እንደነበር ፡ ይተርካሉ ፡፡ ታድያ ፡ በወቅቱ ፡ የነበረው ፡ ማህበራዊ ፤ ታሪካዊና ፡ ፖለቲካዊ ፡ የኑሮ ፡ ሁኔታ ፡ ግንዛቤ ፡ ውስጥ ፡ አስገብተን ፡ ለመረዳት ፡ ካልሞከርን ፡ በርባን ፡ የተባለውን ፡ ማን ፡ እንደነበር ፣ ለምን ፡ ከእስራት ፡ ነጻ ፡ እንዲወጣ ፡ ሕዝቡ ፡ በሙሉ ፡ በጩኸት ፡ ጲላጦስን ፡ አጥብቀው ፡ እንደጠየቁ ፡ ሳንረዳ ፡ እንቀራለን ፡፡ ከዚህም ፡ ባሻገር ፡ በርባን ፡ ማለት ፡ ለሕዝቡ ፡ ምን ፡ አይነት ፡ መሪ ፡ ወይም ፡ ወዳጅ ፡ ወይም ፡ ጠላት ፡ እንደነበር ፡ ሳንረዳው ፡ መቅረታችን ፡ ብቻ ፡ ሳይሆን ፡ እኛም ፡ ሳንረዳው ፡ ቀርተን ፡ እንደ ፡ ወንጀለኛ ፡ ልንቆጥረው ፡ ይችል ፡ ይሆናል ፡፡ በእርግጥ ፡ ቅ. ማቴዎስ ፡ ‹‹ በርባን ፡ በዐመፅ ፡ የታወቀ ፡ እስረኛ ›› (ማቴ 27 ፡ 16) ብሎ ፡ ሲጠቅሰው ፡ ቅ. ማርቆስ ‹‹ ነፍስ ፡ ከገደሉ ፡ ዐመፀኞች ፡ ጋር ፡ የታሰረ ፡ በርባን ፡ የሚባል ፡ አንድ ፡ ሰው ፡ ነበር ›› (ማር 15 ፡ 6) ይላል ፡፡ ቅ. ሉቃስ ፡ ደግሞ ፡ ‹‹በርባን ፡ ከከተማ ፡ ውስጥ ፡ የሕዝብ ፡ ዐመፅ ፡ በማነሣሣትና ፡ በነፍስ ፡ ግድያ ፡ የታሰረ ፡ ሰው ፡ ነበር ›› (ሉቃ 23፡ 19) ሲለው ፡ ቅ. ዮሐንስ ፡ ደግሞ ፡ በአጭሩ ‹‹ በርባን ፡ ወንበዴ ፡ ነበር ›› በማለት ፡ ያልፈዋል (ዮሐ 18 ፡ 40) ፡፡ እዚህ ፡ ላይ ፡ ማስተዋል ፡ ያለብን ፡ በተለይ ፡ የመጀመርያዎቹ ፡ ሦስቱ ፡ ወንጌላት ፡ በርባን ፡ ‹‹በዐመፅ ፡ የታወቀ ፡ እስረኛ›› እንደሆነ ፡ አበክረው ፡ ይገልጻሉ ፡ እንጂ ፡ ለምን ፡ ዐመፀኛ ፡ እንደነበርና ፡ ማን ፡ ላይ ፡ ያምፅ ፡ እንደነበር ፡ አይገልጹም ፡፡ ነፍስ ፡ ከገደሉ ፡ ዐመፀኛ ፡ ሰዎች ፡ ጋር ፡ ታስሯል ፡ ይላሉ ፡ እንጂ ፡ ነፍሰ ፡ ገዳይ ፡ ነበር ፡ ወይም ፡ በነፍሰ ፡ ገዳይነት ፡ ታስሮ ፡ ነበር ፡ አይሉም ፡፡

በእርግጥ ፡ የገዛ  አገሩን፡ ወረው ፡ ይገዙ ፡ የነበሩትን ፡ የሮም ፡ ቀኝ ፡ ገዢዎችን ፡ ይዋጋ ፡ የነበረው ፡ በርባን ፡ በሮማውያን ፡ ዘንድ ፡ እንደ ፡ ወንጀለኛ ፡ ተቆጥሮ ፡ በእስራት ፡ ላይ ፡ ይገኝ ፡ ነበር ፡፡  አገራችንን ፡ በውጭ ፡ ሀይሎች ፡ (በጨቋኝ ፡ ሮማውያን) መገዛት ፡ የለባትም ፤ ሕዝባችንንም ፡ ከሮማውያን ፡ የቀኝ ፡ ግዛት ፡ የጭቆና ፡ ቀንበር ፡ ነጻ ፡ መሆን ፡ አለባት ፡ በማለት ፡ የገዛ ፡ አገሩን ፡ ወረው ፡ የነበሩትን ፡ ሮማውያንን ፡ ማሳደድና ፡ ሕዝቡንም ፡ ለዐመጽ ፡ በመቀስቀስ ፡ የታወቀና ፡ በሕዝቡም ፡ ዘንድ ፡ እንደ ፡ ወንጀለኛ ፡ ሳይሆን ፡ እንደ ፡ ጀግና ፡ ይቆጠር ፡ እንደነበር ፡ የወቅቱ ፡ የህዝቡን ፡ ታሪካዊና ፡ ማሕበራዊ ፡ ሕይወት ፡ ከሚገልጹ ፡ የታሪክ ፡ መጽሐፍቶች ፡ እንረዳለን ፡፡ በሌላ ፡ መልኩ ፡ ደግሞ ፡ እንደ ፡ አንዳንድ ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ሊቃውንት ፡ አገላለጽ ‹‹ በርባን ›› የሚለው ፡ ሥም ፡ ከኢየሱስ ፡ መሞት ፡ ጋር ፡ የተያያዘ ፡ ትርጉም ፡ እንዳለውም ፡ ይገልጹታል ፡፡ ይህም ፡ ‹‹በር-ባን ›› በእብራይስጥ ፡ ቋንቋ ፡ ‹‹የአባት ፡ ልጅ ›› የሚለው ፡ ፍቺ ፡ ሲኖረው ፡ አመፀኛ ፡ የተባለው ፡ በርባን ፡ ነጻ ፡ ወጥቶ ፡ በምትኩ ፡ ኢየሱስ ፡ እንዲሰቀልና ፡ የሞት ፡ ፍርድ ፡ እንዲጎናጸፍ ፡ መደረጉን ፡ ‹‹ በአመፀኞች ፡ ምትክ ፡ የአባት ፡ ልጅ (ኢየሱስ) መሰዋቱን ›› ከሚለው ፡ ጋር ፡ በማያያዝ ፡ ያብራሩታል ፡፡  እነዚህንና ፡ ሌሎችም ፡ ተመሳሳይ ፡ ትንተናዎች ፡ ግንዛቤ ፡ አስገብተን ፡ ስናነበው ፡ የበርባንን ፡ ማንነት ፡ የበለጠ ፡ ግልጽ ፡ እየሆነና ፡ እኛም ፡ መልእክቱን ፡ የበለጠ ፡ ወደ ፡ መረዳት ፡ ልንደርስ ፡ እንችላለን ፡፡

በአጠቃላይ ፡ ከላይ ፡ የተዘረዘሩት ፡ ነጥቦች ፡ ቢያንስ ፡ የተወሰኑትን ፡ እንኳ ፡ ግንዛቤ ፡ ውስጥ ፡ አስገብቶ ፡ አንድን ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ መልእክት ፡ ማንበብ ፡ ወይም ፡ ካነበቡ ፡ በሁዋላ ፡ በተረጋጋ ፡ መንፈስ ፡ እነዚህን ፡ ሀሳቦች ፡ እየከለሱ ፡ መልእክቱን ፡ ለመረዳት ፡ መሞከር ፡ ለመንፈሳዊ ፡ ሕይወታችን ፡ እጅግ ፡ በጣም ፡ ጠቃሚነት ፡ አለው ፡፡ ከዚህም ፡ በላይ ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስን ፡ መልእክት ፡ በጥሩ ፡ ሁኔታ ፡ በተረዳነው ፡ መጠን ፡ እምነታችንም ፡ እየጠነከረ ፡ ከመሄዱም ፡ በላይ ፡ በአንዳንድ ፡ የወንጌል ፡ መልእክቶች ፡ ግራ ፡ ለሚጋቡት ፡ ወገኖቻችን ፡ ብርሃን ፡ ሆነን ፡ ለመምራትም ፡ ይጠቅመናል ፡፡ እንግዲህ ፡ እነዚህን ፡ ነገሮችንና ፡ ሌሎችም ፡ እዚህ ፡ ውስጥ ፡ ያልተጠቀሱትን ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ አጠናን ፡ ዘዴዎች ፡ ግንዛቤ ፡ ውስጥ ፡ በማስገባት ፡ ከላይ ፡ የቀረበውን ፡ አርእስት (ዮሐ 6፡ 1-15 አስማት ፡ ወይስ ፡ ታምራት ) በዝርዝር ፡ በማየት ፡ ለመረዳት ፡ እንሞክር ፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት