እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በእርግጥ ፡ ዐሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ ቁርስራሽ ፡ ተሰብስቧልን?

በእርግጥ ፡ ዐሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ ቁርስራሽ ፡ ተሰብስቧልን ?

አምስት ፡ እንጀራና ፡ ሁለት ፡ ዓሣ ፡ ከአምስት ፡ ሺህ ፡ ሰዎች ፡ በላይ ፡ ከተመገቡት ፡ በኋላ ፡ በእርግጥ ፡ ይህንን ፡ ያህል ፡ ቁርስራሽ ፡ ሊሰበሰብ ፡ ይችላልን ? ወይስ ፡ ሌላ ፡ ትርጓሜ ፡ ሊኖረው ፡ ይችላልን ? ብዙዎች ፡ የመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ሊቃውንቶች ፡ ይህንን « ዐሥራ ፡ ሁለት ›› የሚለው ፡ ቃል ፡ በተለያየ ፡ መልኩ ፡ ሲተነትኑትና ፡ የተለያየ ፡ ትርጓሜ ፡ ሲሰጡት ፡ ይታያል ፡፡ ከእነዚህም ፡ ትንተናዎች ፡ መካከል ፡ እንደ ፡ ምሳሌ ፡ አንዱን ፡ እንይና ፡ የበለጠ ፡ ትርጉም ፡ ሊሰጠው ፡ ይችላል ፡ ወደሚባለው ፡ ሀሳብ ፡ እናትኩር ፡፡ አሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ ዐሥራ ፡ ሁለቱ ፡ የእስራኤላውያን ፡ ነገዶች ፡ የሚያሳይ ፡ ሲሆን ፡ እነዚህ ፡ ነገዶች ፡ በሙሉ ፡  ማለትም ፡ እስራኤላውያን ፡ በሙሉ ፡ ማለት ፡ ነው ፡ ወደ ፡ እኔ (ወደ ኢየሱስ) ቢመጡ ፡ የተትረፈረፈ ፡ የሕይወት ፡ እንጀራ ፡ ያገኛሉ ፡፡ ስለዚህ ፡ ኢየሱስ ፡ የሁሉም ፡ እስራኤላውያን ፡ አዳኝ ፡ መሆኑንና ፡ ለሁላቸውም ፡ ዘላለማዊ ፡ የሆነ ፡ የሕይወት ፡ እንጀራ ፡ ሰጭ ፡ መሆኑን ፡ ለማመልከት ፡ ነው ፡ በማለት ፡ የሚፈቱት ፡ አሉ ፡፡

ከብዙ ፡ ትንታኔዎች ፡ መካከል ፡ ውስጥ ፡ የበለጠ ፡ መልእክት ፡ አስተላላፊነቱን ፡ የሚታመንበት ፡ ግን ፡ ቀጥሎ ፡ የሚገኘው ፡ ሀሳብ ፡ ነው ፡፡ ዐሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ በአሥራ ፡ ሁለቱ ፡ የእስራኤል ፡ ነገዶች ፡ መመሰሉና ፡ የተረፈውንም ፡ ምግብ ፡ ለእስራኤላውያን ፡ በሙሉ ፡ የሚያረካ ፡ የሕይወት ፡ እንጀራ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ መገለጹ ፡ ተገቢ ፡ አይደለም ፤ ምክንያቱም ፡ ኢየሱስ ፡ ለእስራኤላውያን ፡ ብቻ ፡ የመጣና ፡ ትኩረቱ ፡ እነሱ ፡ ላይ ፡ ብቻ ፡ ያደረገ ፡ መስሎ ፡ ያሳያል ፡፡ ይህም ፡ ከእስራኤላውያን ፡ ነገዶች ፡ ውጪ ፡ ላሉት ፡ የኢየሱስን ፡ የአዳኝነት ፡ ተግባር ፡ ወይም « የሕይወት ፡ እንጀራነቱን ›› ለሁሉም ፡ ሕዝቦች ፡ መሆኑን ፡ ይገድባል ፡፡ ስለዚህ ፡ ዐሥራ ፡ ሁለት ፡ መሶብ ፡ ቁርስራሽ ፡ መሰብሰቡን ፡ የሚያሳየው ፡ ኢየሱስ ፡ የሚሰጠው ፡ የሕይወት ፡ እንጀራ ፡ ጊዜያዊና ፡ የሚያልቅ ፡ ሳይሆን ፡ ለዘላለም ፡ የሚኖር ፡ የሕይወት ፡ እንጀራና ፡ እሱንም ፡ የተመገቡት ፡ የሚጠፉ ፡ ሳይሆኑ ፡ ለዘላለም ፡ የሚኖሩ ፡ መሆናቸውን ፡ ለማሳየት ፡ ነው ፡፡ በእርግጥም ፡ ኢየሱስ ፡ ሲያስተምር « አባቶቻችሁ ፡ በምድረ ፡ በዳ ፡ መና ፡ በሉ ፡ ይሁን ፡ እንጂ ፡ ሞቱ ፡፡ ነገር ፡ ግን ፡ ሰው ፡ እንዳይሞት ፡ ይበላው ፡ ዘንድ ፡ ከሰማይ ፡ የወረደ ፡ የሕይወት ፡ እንጀራ ፡ እኔ ፡ ነኝ ፤ ማንም ፡ ሰው ፡ ከዚህ ፡ እንጀራ ፡ ቢበላ ፡ ለዘላለም ፡ ይኖራል ፡ ይህም ፡ እንጀራ ፡ ለዓለም ፡ ሕይወት ፡ እንዲሆን ፡ የምሰጠው ፡ ሥጋዬ ፡ ነው ›› በማለት ፡ አበክሮ ፡ ገልጾታል(ዮሐ 6 ፡ 49) ፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት