Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የአዛኝቱ እመቤታችን ማርያም ታሪክ - መስከረም 5

የአዛኝቱ እመቤታችን ማርያም ታሪክ

Our Lady of Sorrow articleመስከረም 5 - የአዛኝቱ እናት ክብረ በዓል ለረጅም ጊዜ በዓመት ሁለት ጊዜ በ15ኛውና 17ኛው ክፍለ ዘመን በአለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ከደብረ ዘይት በዓል በፊት ያለው አርብ ቀንና በመስከረም ወራት ይከበር ነበር ።

           ይህ የአዛኝቱ ማርያም ክብረ በዓል መሠረት የሆኑት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ሉቃስ 2፡35 ስምዖን የማርያም ልብ በሰይፍ ይወጋል የሚለውና ዮሐ 19፡26-27 ላይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ ለቅድስት ማርያምና ለቅ. ዮሐንስ የተናገረው “እነሆ ልጅሽ” እና “እነሆ እናትህ” የሚሉት ናቸው።     

           ማርያም ያለፍርሃት መስቀል ሥር ሆና ልጇን በሃዘኔታ ትመለከተው ነበር ሌሎቹ ሐዋርያቶች ሰሸሹ። የኢየሱስን ቁስሎች ኀዘን በተሞላበት ዓይኖቿ ተመለከተች። ይሁንና በነዚህ ቁስሎች ለዓለም ደህንነት እንደሆነም አይታልች። ብዙ የቀደምት ዓመታት የቤ/ክ ጸሐፊዎች፣ ይህ ሰይፍ የተባለውን የማርያም ኀዘንና ስቃይ የሚያመለክት ነው ብለው ተርጉመውታል ።

ቅዱስ በርናርዶስ የእመቤታችንን ኀዘን ጥልቀት ሲገልጽ “ሌሎች ሰማዕታት በሥጋቸው ሲሰቃዩ የእርሷ ግን እስከ ነፍሷ ይዘልቃል፤ እሷ ለኢየሱስ ያላት ፍቅር ከማንም በላይ የላቀ፣ የእናትነት ስለሆነ በልጇ ስቃይና ሞት ከማንም የላቀ ኀዘን ተሰምቷታል” ይላል። ቅዱስ አምብሮስዮስ ቅድስት ማርያምን በልጇ መስቀል ሥር ሆና የኀዘን ምልክት መሆኗ ብቻ ሳይሆን እንደጠንካራ የጽናት ተምሳሌትም ሆና ይመለከት ነበር ።

ትርጉም፦ ዮሴፍ ወልደዮሐንስ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።