የመጨረሻው ምስጋና
- Category: በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ጸሎት ሰባት ልመናዎች
- Published: Thursday, 13 October 2011 19:19
- Written by Super User
- Hits: 4602
- 13 Oct
የመጨረሻው ምስጋና
የመጨረሻው ምስጋና “መንግሥት፣ ኃይልና ክብር አሁንም ለዘላለም የአንተ ናቸው” የሚለው ሃረግ ለአባታችን የሚቀርቡትን የመጀመሪያዎቹን ሦስት ልመናዎች፣ ማለትም የስሙን መቀደስ፣ የመንግሥቱን መምጣትና የአዳኝ ፍቃዱን ኃይል አጣምሮ እንደገና ይጠቅሳል፡፡ በሰማያዊው ስርአተ አምልኮ እንደተንፀባረቀው እነሆ አሁን እኒህ ጸሎቶች እንደ አምልኮና ምስጋና ይቀርባሉ፡፡ የዚህ አለም ገዥ ንጉሥነትን፣ ሥልጣንና ክብርን፣ ለራሱ በሃሰት ሰጥቷል፡፡ የድኅነት ምስጢር ከፍጻሜ በሚደርስበትና እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ በሚሆንበት ጊዜ መንግስቱን ለእርሱ እስከሚያስረክብ ድረስ ጌታ ክርስቶስ ማእረጋቱን ለእርሱና ለእኛ አባት ያስረክባቸዋል፡፡”1ቆሮ 15፡24-28
ከዚያም ጸሎቱ ከአበቃ በኋላ “አሜን” እላላችሁ፤ ትርጉሙም ይሁን ማለት ሲሆን እግዚአብሔር በአስተማረን ጸሎት ውስጥ ተጠቃልሎ የሚገኘውን በእኛ “አሜን” ማለት እናጸድቀዋለን፡፡”