3 - ክብራችንና የሕፃናት ክብር

3 - ክብራችንና የሕፃናት ክብር

የእግዚአብሔር ቃል፤ - የመልአኩ ገብርኤል ብሥራት፤ ሉቃስ 1፡ 26-38

‹‹መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ የልዑል እግዚአብሔርም ኀይል በአንቺ ላይ ይሆናል፤ ስለዚህ ከአንቺ የሚወለደው ሕፃን ቅዱስ ነው፤ የእግዚአብሔርም ልጅ ይባላል››፡፡ ማርያም ‹‹እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነኝ፤ አንተ እንዳልህ ይሁንልኝ›› አለችው፡፡

መንፈስ ቅዱስ በማርያም ላይ መጣ፡፡ እንደ መንፈስ ቅዱስ ፍሬ ቅድስት ማርያም፤

የእናም ቤተሰብ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሏል፡፡ በምስጢረ ጥምቀት፣ ሜሮን፣ ቅዱስ ቁርባን፣ ተክሊልና በጸሎታቸው አማካይነት የቅድስት ሥላሴ ቤተ መቅደስ ናቸው፡፡ የእኛም ልጆች ቅዱሳንና የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር የፍቅር ፍሬዎች ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ሕፃን እግዚአብሔር ለእኛ የላከ መልዕክት፣ ደብዳቤና ሥጋ የለበሰ ቃል ነው፡፡ ኢየሱስ ፍፁም የእግዚአብሔር የተላከ መልዕክት ነው፡፡ ይህንን መልዕክት ልንረዳው፣ ልንሰማው እና ልንቀበለው ዝግጁዎች ነን?

እያንዳንዱ ሰው ወደ ዓለም የሚመጣው ጥሩ ተልኮ ለመፈፀም ነው፡፡ እያንዳንዱ ሰው ወደ ዓለም ሲመጣ እግዚአብሔር አንድ ስም (ንጽ. የሐ ራዕይ 2፡ 17)፣ አንድ ጥሪ ይሰጠዋል፡፡ ወደ አባታችን ስንመለስ በዚህ ዓለም ላይ የገነባነው ስም (እዚህ የገነባው ጥሩም ሆነ መጥፎ ተልዕኮ) እግዚአብሔር የሰጠንን ስም (እግዚአብሔር ለእኛ አስቦልን የነበረው ተልዕኮ) ይነጻጸራል፡፡ ሙሉ ደህንነት ልናገኝ የምንችለው ስማችን (ተልዕኮአችንን ከፈፀምን) እግዚአብሔር ከሰጠን ስም ጋር ተመሳሳይ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ሕይወት የዚህ ስም ፍለጋና እግዚአብሔር ከእኛ ምን እንደሚፈልግ የምንረዳበት ነው፡፡ እመቤታችን የእርሷ ተልዕኮ ስለተረዳች ‹‹አንተ እንዳልህ ይሁንልኝ›› ብላ መልሳለች፡፡

ሕፃንን ልንቀበለው፣ ልናከብረው፣ ለናገለግለውና በክርስቲያናዊ ጥሪ መሰረት እንዲያድግ ልናገዘው ዝግጁዎች ነን ወይ?

‹‹ ›› (ማር 9፡ 36-37)፡፡

አንድ የክርስቲያን ቤተሰብ ለልጆቹ የሚያስፈልገውን መሰረታዊ መብት፤ እምነት፣ ትምህርት፣ ምግብ፣ ጤናቸውን መጠበቅና ክብር መስጠት ችላ ብሎ፣ እንዴት ልጆቹን በመጥፎ አያያዝ፣ አጎሳቁሎ፣ በቸልተኝነት፣ ለራስ ጥቅም ብቻ ሥራ በማሰራት ያሳድጋል?

‹‹ ›› (ማር 9፡ 42)

እያንዳንዱ ሕፃን የቅድስት ሥላሴ ቤተ መቅደስ መሆኑን እናምናለንና እያንዳንዱን ሕፃን የቅድስት ሥላሴ ቤተ መቅደስ መሆኑን እናምናለንና እያንዳንዱን ሕፃን በአክብሮት መያዝ አለብን፡፡ ይህ ባሕላችን ስለሆነ ለዚህ ምስክርነት መስጠት አለብን፡፡

እንጸልይ፡-

የክርስቶስ አባት የሆንክ እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዝቅተኛ ቦታ አንስተህ የአዳኝ እናት በማድረግ ኃይልህን ገልጠሃል፡፡ የቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት ክርስቶስን እየጠበቀ ላለው ዓለማችን እርሱን እንዲያመጣና ሙሉ ያልሆነውን ዓለማችን በለጇ እንዲሞላ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡