ግንቦት 26 2004 ዓ.ም - ቡሩክ በዓል ጰራቅሊጦስ

ግንቦት 26 2004 ዓ.ም - ቡሩክ በዓል ጰራቅሊጦስ

1ቆሮ 15፡ 2ዐ-34 1ጴጥ 1፡1-12 ዮሐንስ 2ዐ፡1-23

ሁለት ነጫጭ ልብስ የለበሱ መላእክት ጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በተቀበረበት መቃብር እግርጌና እራስጌ ተቀምጠው አንቺ ሴት ስለምን ታለቅሻለሽ ብለው ማርያምን ይቀይቋታል፤ ጌታዬን ወስደውታል ወዴት እንዳኖሩት አላውቅም ብላም ትመልስላቸዋለች ያንጊዜ ነበር ኢየሱስ "ማርያም" ብሎ ጠራት እርሷም ዘወር ብላ ረቡኒ በዕብራይስጥ መምህር ማለት ነው" ነጫጭ ልብስ የለበሱት መላእክት እንደ አለባበሳቸው ደስታን አብሳሪ ብርሃንን ፈንጣቂ ተስፋን የሚገልጥ መልዕክትን የያዙ ናቸው፡፡ በደስታ ተሞልተው ደስታን የሚያበስሩ ዛሬም መላዕክቱ ደስታን የሚያበስሯት መግደላዊት ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰባት አጋንንት ያወጣላትንና ከስቃይ ካዳናት በኋላ የክርስቶስ አገልጋይ የነበቀበሩ ምና የመረች ስትሆን የስቅለስክር የሆነች እንዲሁም ከሞት ከተነሳ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ክርስቶስ የታያት ትልቅ አገልጋይ ነበረች፡፡ የዛሬውም ወንጌል ይህንኑ በሰፊው ያሳየናል፡፡ ማርያም መግደላዊት የተደረገላትን ውለታ ቆጥራ የክርስቶስ አልጋይ ነበረች እስከመስቀሉና ሕማማቱን ተካፍላለች፡፡ ከእነዚህ አገልጋዮች ዛሬ እኛ ልንማር የሚገባን ብዙ ነገሮች አሉን፡፡ ማርያም መግደላዊት ከጌታችን ከመድኃኒታችን ስር ስር እየተከተለች ስቃዩን ሁሉ ተካፋይ ነበረች፡፡ ዛሬ እኛስ የወንድሞቻችን ችግር፣ ሐዘን፣ ሕመም እንካፈላለን ዋናው ከክርስቶስ ጋር መሆንና የክርስቶስን ሕይወት ተካፋይ ከሆንን የነዚህን የወንድሞቻችንን ነገሮች ሁሉ መሸከም ይገባናል፡፡

ምንባቡ ስለ ምን ይናገራል?

እንደ ማርያም መግደላዊት ተደረገልንን እናውቃለን?