5 - የእናት አገልግሎት

5 - የእናት አገልግሎት

የእግዚአብሔር ቃል፤ - እመቤታችን ማርያም ኤልሣቤጥን ጎበኘች፡፡ ሉቃስ 1፡ 39-45

ማርያም ኤልሳቤጥን ለመጎብኘትና ለማገልገል በተራራማው በይሁዳ አገር ወዳለችው ከተማ በፍጥነት ተነሥታ ሄደች፡፡

ማርያም የእግዚአብሔርና የእኛ አገልጋይ ናት፡፡

እናት ከፍቅሯ የተነሣ ሁል ጊዜ ታገለግላለች፣ ከባሏና ከልጆቿ ምንም አትጠብቅም፡፡ የእርሷ ደስታ እነርሱ ሲያድጉ ማየት ነው፡፡ አገልግሎት እናመሰግናቸዋለን? ይህ አገልግሎት የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ ነው፤ መንፈስ ቅዱስ በእናቶቻችንና በሌሎች በሚያገለግሉት ሁሉ ላይ የመሆኑ ምልክት ነው፡፡

በሕብረተሰባችን ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው ማገልገል የሚፈልጉ፡፡ በቤተሰባችን ውስጥም አንዱ አንዳንድ ጊዜ ማገልገልን ሳይሆን አለቃ መሆንን ይመርጣል፡፡ ኢየሱስ ግን ሁሉንም ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፡፡

‹‹ ›› (ማቴ 20፡ 25-28)፡፡

‹‹ ››(ዮሐ 13 12-15፣34)፡፡

ኢየሱስ የአገልግሎት ትእዛዝ ሁሉ በእናቱ በማርያም እንደተፈጸመ አይቷል፡፡ እርሱ፣ እንደ ሌሎች ልጆች፣ ፍፁም ሰው ስለሆነ፣ ከእናቱ ማገልገልን ተማረ፡፡ የእናት መስዋዕትነትና ጥሩ ምሳሌነት በቤት ውስጥ ፍሬ ያፈራል፡፡

እንጸልይ፡-

ዘላለማዊ አባት ሆይ፣ ቅድስት ድንግል ማርያም የልጅህ እናት እንድትሆን ቅድስት ኤልሳቤጥንም በሚያስፈልጋት አገልግሎት እንድታገለግልና እንድትጎበኛት በመንፈስህ ሞላኃት፡፡ እኛንም ለመንፈስ ቅዱስ ስራ ልባችንን ክፍት አድርገህልን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ሁሌ አንተን እንድንወድስህ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃለን፡፡ አሜን፡፡