Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በወንጌል የሕይወት ጎዳና በክርስቶስ መኖር

4በጥሩ ሁኔታ የታነጸ የምንኩስና ጥ በቁጥር ብዙ ከሆነው ጥሪ የበለጠ ጠቃሚ ነው ሲሉ ር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ ባለፈው ቅዳሜ በቫቲካን ለተሰበሰቡ የምንኩስና ጥሪ ላይ በኀላፊነት ለሚያገለግሉ ተጋባእያን አሳሰቡ።

“የምንኩስናን ሕይወት ውበት በሕይወት ማስተላለፍ ስኬታማነት ባለበት ቦታ የጥሪ መቃወስ የለም፤ የምንኩስና ሕይወት በተዳከመበት ቦታ ቢሆንም እንኳ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ነገር እጩዎችን ማብዛት ሳይሆን የአያያዙ ጥራት ላይ መሆን አለበት” ብለዋል ር.ሊ.ጳ.።

“በወንጌል የሕይወት ጎዳና በክርስቶስ መኖር” በሚል ርእስ ከመጋቢት 9 እስከ ሚያዝያ 3 በተደረገው የአምስት ቀናት ኮንፈረንስ 1300 የሚሆኑ የምንኩስና ጥሪ ኀላፊዎች ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል። ር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ ለነዚሁ ተሳታፊዎች በሥራቸው እንክብካቤ ለሚገኙት ወጣት እጩዎች ያላቸውን ልዩ ፍቅርና የዚህን አገልግሎት ወሳኝነት ገልጸዋል።

“የምንኩስና ሕይወት ውብ ነው። በጥምቀት ጥሪ ውስጥ የተተከለ የቤ/ያን የከበረ ሀብት ነው” በማለት ስለ ምንኩስና ሕይወት ምንነት ተናግረዋል። አያይዘውም በዚህ የምንኩስና ጥሪ ላይ በኀላፊነት የሚያገልግሉ ሁሉ መንፈስ ቅዱስ በጠራቸው ውስጥ የልጁን ልብ ከሚያትመው ከእግዚአብሔር አብ ሥራ ጋር በልዩ መብት ተሳታፊ መሆናቸውን አስታውሰዋል። እንዲሁም እነዚሁ ኀላፊዎች በሥራቸው ለተሰጡ ወጣቶች እውነተኛ እናቶችና አባቶች እንዲሆኑና የሰፊ ልብ ባለቤት በመሆን ሀሉንም መቀበል የሚችሉ ልበ ሰፊ የሆኑ መነኮሳትን ማዘጋጀት እንዲችሉም አደራ ብለዋል።

በስተመጨረሻም ር.ሊ.ጳ. ለምንኩስና የማዘጋጀት ኀላፊነት ከሌላ ተግባራት ቢገታቸውም ኀላፊዎቹ ይህ አገልግሎት ሸክም እንደሆነ እንዳያስቡ አስገንዝበው፤ “ቤተ ክርስቲያን እናንተን ትወዳችኋለች፣ ትጸልይላችኋለችም፤ ያለእናንተ አገልግሎት የምንኩስና ሕይወት አይኖርም” በማለት ደምድመዋል።

ምንጭ፡http://www.catholicnewsagency.com/news/pope-francis-vocations-are-about-quality-not-quantity-20907/

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።