Map St Joseph Cistercians

Top Panel

መላዪቱ ቤተ ክርስቲያንና ር.ሊ.ጳ. ከስደተኞች ጎን

Zenit.org - ከሊቢያ ተሰድደው ወደ ጣልያን ሲያመሩ በነበሩት 250 ስደተኞች ድንገተኛና ዘግናኝ  ሞት ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ጥልቅ ልባዊ ኀዘን የተሰማቸው መሆኑን ቫቲካን ቃል አቀባይ ገለጹ።

ረቡዕ መጋቢት 29 ቀን 2003 ዓም  ማለዳ 300 ሰዎችን ያጎረች ጀልባ በሊቢያ ያለውን ግጭት ለማምለጥ ወደ ጣልያን በማምራት ላይ ሳለች የመስመጥ አደጋ የደረሰባት ሲሆን በጀልባይቱ ውስጥ ከነበሩት ተጓዦች በሙሉ 50 ሰዎችን ብቻ በሕይወት መታደግ ሲቻል ከሞቱት ውሰጥም ሕፃናት ይገኙበት እንደነበር ታውቋል።

ኢየሱሳዊው ካህን አባ ፌዴሪኮ ሎምባርዲ የቫቲካን ማስታወቂያ ቢሮ ኀላፊ አሳዛኙ አደጋ የር.ሊ.ጳ.ን ልብ በእጅጉ እንደነካ ለጋዜጠኞች ጠቅሰው

በዚህ በተለየ ሁኔታ ለስደተኞች አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ ቅዱስ አባታችን የስደተኞችን ጉዳይ ከቅርብ በመከታተል ላይ መሆናቸውን አሳውቀዋል። በዚህ የሜዲትራንያን ባሕር አደጋ ሰለባዎች መካከልም የተወሰኑት በሊቢያ ካቶሊካዊ ማኅበረሰብ ውስጥ ተሳትፎ የነበራቸው ኤርትራውያን ካቶሊኮች ይገኙበት እንደነበረም ተገልጿል።

የድኽነትን ወይም የኢፍትሐዊነትን፤ የአመፅን ወይም የጥቃትን ሁኔታዎች በመሸሽ የሚቀበላቸውን፣ የሚከላከላቸውንና የበለጠ ሰብአዊ ሕይወትን ለመፈለግ ሲሉ በአስቸጋሪ ጉዞ ሕይወታቸውን የሚያጡትን የዚህን ዓይነት አደጋ ሰለባዎች፤ የማንኛውንም አገር ዜጎች ሕፃናትንና ሴቶችን ሁሉ ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስና መላዪቱ ቤተ ክርስቲያን በጸሎት እንደሚያስታውሷቸውም አሳውቀዋል።

ባለፈው ሳምንት ብቻ የተለያየ አገር ዜግነት ያላቸው 22 ሺህ በሊቢያ ያለውን ጦርነት በመሸሽ ወደ ጣልያን የባህር ዳርቻዎች መድረሳቸውም ተዘግቧል።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።