Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛውና የእረፍት ጊዜያቸው

The Pope writeswww.catholicnewsagency.com - ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ ፲፮ኛው በዚህ ወቅት የእረፍት ጊዜያቸውን በሚያሳልፉበት ከሮም ውጭ በሚገኘው ካስተል ጋንዶልፎ ሆነው በናዝሬቱ ኢየሱስ ላይ የሚጽፉትን መጽሐፍ ሦስተኛ መድበል ጽፈው መጨረሳቸውን ቫቲካን የማስታወቂያ ቢሮ ገለጸ።

ይህ መድበል በክርስቶስ የሕፃንነት ሕይወት ላይ የሚያተኩር መሆኑ ሲገለጽ የዚህ መጽሐፍ ሁነኛ እትም በጀርመንኛ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ወደተለያዩ ቋንቋዎች በመተርጎም ላይ ይገኛል፤ ይህ በዐበይት ቋንቋዎች የመተርጎሙ ሂደት ሲጠናቀቅም ለሕትመት እንደሚበቃ ታውቋል።

አዲሱ መድበል "የናዝሬቱ ኢየሱስ" በሚል ርእስ በ1999 ዓ.ም. የታተመውና በ2003 ዓ.ም. "የናዝሬቱ ኢየሱስ - ከኢየሩሳሌም መግባት እስከ ትንሣኤ" በሚል ርእስ የወጣው የሁለቱ ሥራዎቻቸው ቀጣይ ሦስተኛ መጽሐፍ ነው። ሁለቱ መጻሕፍታቸው በሰባት ቋንቋዎች በወረቀትና በኤሌክትሮኒክ መልኩ ለሕዝብ የቀረቡ ሲሆን ከአንድ ሚሊዮን ቅጂዎች በላይ መሸጣቸው ታውቋል።

በዚሁ በእረፍት ጊዜያቸው ይህን መጽሐፍ ከማጠናቀቅ ባሻገርም ር.ሊ.ጳ. ከመስከረም 4 እስከ 6 ድርስ በሊባኖስ ለሚያደርጉት ሐዋርያዊ ጉብኝትም ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆናቸውና ምናልባትም ከዚህ የመጽሐፍ ሥራቸው በኋላ አራተኛ የሚሆነውን ለመላዪቱ ቤተ ክርስቲያን የሚሆን አንድ የእምነት አንቀጽን የሚመለከት መልእክት Encyclical letter ሊያዘጋጁ እንደሚችሉ ይገመታል።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።