በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ የመነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት ሕንድ ትመራለች
- Category: ዜናዎች
- Published: Monday, 14 December 2009 19:54
- Written by Super User
- Hits: 2323
- 14 Dec
Independent Catholic News - በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የመነኮሳውያት (የእማሆዮች) የቅርብ ዓመታት ቁጥራዊ ዕድገት ሕንድ ግንባር ቀደሙን ቦታ መያዟ ተገለጠ።
የ"Catholic Culture" ድረ ገጽ ባደረገው አኀዛዊ ዳሰሳ መግለጫ መሠረት ባጠቃላይ ሲታይ እስያና አፍሪካ እ.ኤ.አ. ከ2000 ዓ.ም. ጀምሮ ጥሩ የመነኮሳውያት ቁጥር መጨመር ሲታይ፤ በአውሮፓ፣ አሜሪካና ኦሺኒያ የቁጥር ማቆልቆሉ ታውቋል።
እ.ኤ.አ. ከ2002-2007 ዓ.ም. በእስያ ውስጥ ሕንድ የ9,838 ፣ ቬትናም የ2,545 እንዲሁም ፊሊፒንስና ደቡብ ኮሪያ እያንዳንዳቸው የ500 መነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት አሳይተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የመነኮሳውያት ቁጥር ዕድገት ካሳዩት ማኅበራት ውስጥ ሦስት በከራላ (ሕንድ) ውስጥ የተመሠረቱና የብፅዕት እማሆይ የፍቅር ልኡካን እህቶች ላቅ ያለውን ስፍራ ይይዛሉ።
ይህም ቢሆን ግን ቅሉ በጥናታዊው ዳሰሳ መሠረት በመላው ዓለም ያለውን የመነኮስውያት ብዛት እ.ኤ.አ. ከ2002-2007 ዓ.ም.በ4.6 በመቶ መቀነስ ሊያስቀረው አልቻለም።
በምዕራቡ ዓለም ግን በጣም ከፍተኛ በሆነ ሁኔታ ቁጥሩ ቀንሷል። ከላይ በተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ በጣልያን የ11,156 መነኮሳውያት ቁጥር ሲቀንስ በተመሳሳይ ጊዜም ሰሜን አሜሪካ የ10,454 መነኮሳውያት ቅነሳ ታይቷል።