እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

2 - እኛ በእግዚአብሔር የተወደድን ነን

2 - እኛ በእግዚአብሔር የተወደድን ነን

የእግዚአብሔር ቃል፤ - የመልአኩ ገብርኤል ብስራት፣ ሉቃስ 1፡ 26-38

‹‹አንቺ ጸጋ የተሞላሽ፤ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝተሻልና አትፍሪ››፡፡

እነዚህ ቃላት ለእያንዳንዳችን ይደገሙልናል፡፡ ማርያም ለእኛ ምሳሌ ናት፡፡ በማርያም እግዚአብሔር በእኛ ላይ ያለው የፍቅር ዕቅድ ተፈጽሞአል፡፡ እመቤታችንን በመመልከት እግዚአብሔር እያደረገና ሊያደርግ ያሰበውን ነገር በይበልጥ እንገነዘባለን፡፡ ወደ ኤፌሶን ሰዎች የተላከውን መልእክት እናዳምጥ፤ ‹‹ ›› (ኤፌ 1፡ 3-6)፡፡

እነዚህን ሁለት ጥቅሶችን ማወዳደር እንቸላለን፡፡

ሉቃስ 1፡ 26-47

ኤፌ 1፡ 3-6

1

‹‹አንቺ ከሴቶች ሁሉ የተባረክሽ ነሽ፤ ከአንቺ የሚወለደውም ልጅ የተባረከ ነው፤ የጌታዬ እናት ልትጎበኘኝ መምጣትዋ ለእኔ እንዴት ያለ ታላቅ ክብር ነው››፡፡

‹‹በሰማይ መንፈሳዊ በረከትን በመስጠት በክርስቶስ የባረከን››

2

‹‹ነፍሴ ጌታን ታከብራለች መንፈሴ በአምላኬ በመድኃኒቴ ትደሰታለች››፡፡

‹‹የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት የሆነው አምላክ ይመስገን››

3

‹‹አንቺ ጸጋን የተሞላሽ፤ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝተሻል››

‹‹ቅዱሳንና ነቀፋ የሌለብን ሆነን በፊቱ እንድንገኝ ዓለም ሳይፈጠር በክርስቶስ መረጠን››

4

ማርያምም በክርስቶስ ደም በፀጋ ተሞልታለች

‹‹በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ልጆቹ እንድንሆን አስድሞ ወሰነን፡፡ ይህንንም ያደረገው በተወደደው ልጁ አማካይነት በነፃ የሰጠን ክቡር ጸጋ እንዲመሰገን ነው››

ቅድስት ድንግል ማርያምን በማክበር የእግዚአብሔር ፍቅር በአንድ ሰው ውስጥ ምን ማድረግ እንደሚችል ልንረዳ እንችላለን፡፡ ማርያም፣ እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ የለው መጥፎ ነገር ማሸነፍ እንደሚችል፣ ማስረጃ ናት፡፡ ይህም የሚሆነው እኛም እንደ ማርያም ሕይወታችንን ከሰዋንለት ነው፡፡

የቤተሰባችን አባላት በሙሉ፤ አባት፣ እናት፣ ልጆች፣ ወጣቶች፣ ሽማግሌዎችና የታመሙ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት የተወደዱ ናቸው፡፡ ማንም ሊናቅ፣ ሊጣል፣ ሊረሳ፣ ሊረገጥ፣ ሊዋረድና ሊገለል አይችልም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የሚለንን እንስማ፤

‹‹ ›› (ሲራክ 3፡ 3-5፣ 12-14)

እንጸልይ፡-

እግዚአብሔር አባት ሆይ፣ ቃል ሥጋ በመሆን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ እኛም እውነተኛ አምላክና ሰው፤ አዳኝ የሆነውን ክርስቶስን እንድንመስል እርዳን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንለምንሃን፡፡ አሜን፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት