የርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አስተምህሮ
- Category: ዜናዎች
- Published: Wednesday, 17 June 2009 00:00
- Written by Super User
- Hits: 2184
- 24 Jun
ቅ.አ.ር.ሊ.ጳጳሳት በነዲክቶስ 16ኛ ዛሬ በቅ.ጴጥሮስ ባዚሊካ አደባባይ ለተሰበሰቡት ብዙ ምእመናን ባሰሙት አስተምህሮ በቅርቡ ወደ ቅድስት መሬት አድርገውት ስለ ነበረው ሐዋርያዊ ጉብኝት በሰፊው ገልጠው ምእመናን ለመካከለኛው ምሥራቅ ቤተክርስትያን እና አገራት ሰላምና ብልጽግና አብረዋቸው እንዲጸልዩ ጠይቀዋል፣ ለጉብኝቱ መሳካት ለተባበሩትና ለረዱት ሁሉም ከልብ አመስግነዋል።
በፊታችን እሁድ በቤትክርስትያን ተስታውሶ የሚውለውን ዓለም አቀፍ የግኑኝነቶች ቀን በመጥቀስም በተለይ ወጣቶች የዘመኑ ሥልጣኔ ውጤት የሆነውን የግኑኝነት ጥበብ ጓደኝነትን ኅብረትን ምሕረትንና የሰላም ውይይትና ባህልን በሚያጎልብቱ አዎንታውያን ግቦች ላይ ለመድረስ እንዲጠቀሙበት አደራ ብለዋል።
በጉባኤ አስተምህሮው መጨረሻም በሥርዓቱ ላይ ለተሳተፉት ምእመናን በተለያዩ ቋንቋዎች ሰላምታና ሐዋርያዊ ቡራኬ አቅርበው በሰላም ወደየመጡበት አሰናበቱ።