ፍቅር “ይኖራል፣ በመኖሩም ነገሮችን ይለውጣል”
- Category: ዜናዎች
- Published: Monday, 15 June 2009 22:07
- Written by Super User
- Hits: 5032
- 15 Jun
ቅ.አ.ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ 16ኛ ትናንት እሁድ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት ከመምራታቸው በፊት ዕለቱ በዛ ባሉት አገሮች ኮርፑስ ዶሚኒ በዓለ (ቅዱስ ቍርባን) ተከብሮ የሚውልበት ቀን መሆኑን አስታውሰው መላው ዓለም በረሃብ በመሰቃየት ላይ ያሉትን በሚሊዮናት የሚገመቱ ሕዝቦች ጉዳይ መረሳት እንደሌለበት አሳሰቡ።
ቅዱስነታቸው በፊታችን ሰኔ ሃያ አራትና ሃያ ስድስት በኒዮርክ ስለ ምጣኔ ሃብትና ገንዘብ መቃወስ ችግር መፍትሔ ለመሻት ሊካሄድ ታቅዶ ያለውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጉባኤ ጠቅሰው የረሃቡ ክስተት ጉዳይ ጨርሶ ተቀባይነት የሌለው ምክንያት አልባ ክስተት መሆኑን አስጠነቅቀዋል። በመጨረሻም ምእመናን በፊታችን ዓርብ ስለ ሚጀመረው የክነት ዓመት እንዲጸልዩ ጠይቀዋል።