ር.ሊ.ጳ. ስለ ኢየሱስ አያቶች
- Category: ዜናዎች
- Published: Monday, 27 July 2009 15:27
- Written by Super User
- Hits: 2533
- 27 Jul
ቅ.አ.ር.ሊ.ጳ. ቤኔዲክቶስ 16ኛ ትናንት እሑድ ለበጋው ዕረፍታቸው ከሚገኙበት በለኮምበስ መንደር መኖሪያ ቤታቸው አጠገብ ከሚገኘው አደባባይ የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት መምራታቸው እና መንፈሳዊ መልእክት ማስተላለፋቸው ተመለከተ።
ቅዱስነታቸው ትናንትና የላቲን ሥርዓት በምትከተለው ቤተ ክርስትያን ዕለቱ የቅዱሳን ኢያቄም እና ሃና የኢየሱስ አያቶች ማለት የቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች በዓል መሆኑን አስመልክተው በዓለም ዙሪያ ለሚገኙት አያቶች ሁሉ ለልጅ ልጆቻቸው በማስተማር ዘርፍ ላላቸው ኃላፊነት እና ለሚሰጡት ከፍተኛ ክቡር አገልግሎት አመስግነዋል።