እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ማርያምን ተመልከት፣ ጥራትም፣ አትጠፋምና!

ማርያምን ተመልከት፣ ጥራትም፣ አትጠፋምና!

Bernard Maryጌታችን በቅዱስ መስቀሉ ላይ ሳለ ለሰው ልጆች በሙሉ ሊሰጥ ያለውን  ልዩ ስጦታ በሐዋርያው ዮሐንስ በኩል አደረገው፤ እናም «ይህችውልህ እናትህ አለ፣ ለእርሷም እነሆ ልጅሽ» በማለት በእመቤታችንና በተከታዮቹ መካከል ያለውን የልጅና የእናትነት ትስስር በጉልህ አሳየ። በዮሐ. 19፡26-27 ላይ እንደምናነበው ቅ. ዮሐንስም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ወደ ቤቱ ወሰዳት። ከዚያን ሰዓት ጀምሮ እስከ እድሜያችን ብዙ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች የዮሐንስ ወንጌላዊውን አደራ ተረክበው፣ የክርስቶስ በመሆናቸው እናቱንም እናታቸው በማድረግ በሕይወታቸው የእርሷን አብነትና አማላጅነት እንደ ትልቅ ትሩፋት ኖረው አልፈዋል። እመቤታችንም እናት የመሆን አደራዋን ልጅ ለሆኑላትና ለቀረቧት ከልጇ ጋር እያጣመረች ታቅፋቸዋለች። ከነዚህ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶች አንዱና «የእመቤታችን ዘማሪ» በመባል የሚታወቀው የ12ኛው ክ.ዘ. ቅ. በርናርዶስ ዘክለርቮ (ሲታዊ) ይጠቀሳል (ክብረ በዓሉ ነሐሴ 14 ነው)። በልዩ የአጻጻፍና አገላለጽ ዘዬው ስለእመቤታችን ማርያም ልዩ መንፈሳዊ ሥልጣንና ርኅራኄ በመደነቅ ልጇንና ጌታዋን በታማኝነትና በፍቅር ባሳደጉ፣ በያዙ እጆቿ መያዝን እንመርጥ ዘንድና እርሷ እናታችን ክርስቶስንም ወንድማችን ይሆኑ ዘንድ እንዲህ አለ፡-

  • ማርያም ማለት የባሕር ኮከብ ማለት ነው። እንግዲህ አንተ በዚህ ዓለም ውስጥ በደረቅ መሬት ላይ ሳይሆን በማዕበልና በአውሎ ነፋስ መካከል የምትሄድ ሰው ሆይ! በማዕበሉ እንዳትሰምጥና በአውሎ ነፋስ እንዳትወሰድ ከፈለግህ ዓይንህን ከዚህች ኮከብ ብርሃን አታርቅ።
  • የፈተና ማዕበል ከተነሣብህ፣ የጭንቀት ዓለት ካጋጠመህ ወደዚህች ኮከብ ተመልከት፣ ማርያምን ጥራት።
  • የትዕቢት፣ የቅናትና የክብር ፍላጎት አውሎ ነፋስ ካናወጠህ ይህችን ኮከብ ተመልከት፣ ማርያምን ለምናት።
  • ቁጣ፣ ንፍገትና የሥጋ ፍትወት ነፍስህን ከረበሻት ማርያምን ተመልከት።
  • በኃጢአትህ ብዛትና በኅሊናህ መቆሸሽ ምክንያት በእግዚአብሔር ፍርድ ቀን ደንግጠህ በኀዘንና በተስፋ መቁረጥ መስጠም ከጀመርህ ማርያምን አስብ፣ አስታውሳትም።
  • በአደጋና በችግርህ ጊዜ፣ በጥርጣሬህም ጊዜ ማርያምን አስባት፣ ማርያምን ጥራት።
  • እርስዋ ከአፍህ አትለይ፣ ከልብህም አትራቅ።
  • የጸሎትዋን እርዳታ እንድታገኝ የሕይወት አርአያዋን ተከተል።
  • እርስዋን ከተከተልህ መንገዱ አይጠፋህም፤ ከለመንሃትም ተስፋ አትቆርጥም። እርስዋን ካሰብህ አትሳሳትም፣ እርስዋ ከያዘችህ አትወድቅም።
  • እርስዋን ከተጠጋህ አትፈራም፣ እርስዋ ከመራችህ አትደክምም። እርስዋ ወደ ልጅዋ /ወደ መንግሥተ ሰማያት/ ታደርስሃለች። 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት