እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በፍቅር መጽናት

በፍቅር መጽናት

"ባለመቋረጥ ጸልዩ፣... በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ሁሉ ነገር እግዚአብሔር አብን ዘወትር አመስግኑ፡፡" 1ተሰ.5፡17፤ኤፌ5፡2ዐ ቅዱስ ጳውሎስ "በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ሰለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤" ኤፌ 6፡18 ሲል ያክልበታል፡፡ ምክንያቱም "ያለማቋረጥ ለመሥራት፣ ነቅተን ለመጠበቅና ለመጾም አልታዘዝንም ነገር ግን ያለማቋረጥ እንድንጸልይ ተደንግጓል፡፡ ይህ መታከት የማይታይበት የጋለ ስሜት ሊመጣ የሚችለው ከፍቅር ብቻ ነው፡፡ ከእኛ ቀዝቃዛነትና ስንፍና አንፃር የጸሎት ውጊያ ትህትና፣ እምነትና ጽናት የተላበሰ ፍቅር ነው፡፡ ይህ ፍቅር ልባችን እምነትን በሚጠቁሙ አስረጂና ገላጭ ሕይወት ሰጪ በሆኑ ሦስት ቁም ነገሮች ላይ እንዲያተኩር ያደርጋል፡፡

ሁልጊዜ መጸለይ ይቻላል፡- የክርስቶስ ዘመን፣ ምንም ዓይነት ማዕበሎች ይነሡ ሁልጊዜ ከእኛ ጋር የሆነው የተነሣው ክርስቶስ ነው፡፡ ጊዜአችን በእግዚአብሔር እጅ ነው፡፡

በሕዝብ መካከል በምትሄዱበት ወይም በእግር በምትጓዙበት ወይም በመደብራችሁ ውስጥ በመግዛት ወይም በመሸጥ ላይ እያላችሁ፡ ... ወይም ምግብ በምታበስሉበት ሰዓት እንኳ የጋለ ልባዊ ጸሎት ማቅረብ ትችላላችሁ፡፡ St. John Chrysostom, Ecloga de oratione

ጸሎት እጅግ አስፈላጊ ነው፡- በተቃራኒው ያለው ማረጋገጫም አሳማኝነቱ ከዚህ የተነሳ አይደለም፤ መንፈስ ቅዱስ እንዲመራን ካልፈቀድን፣ ወደ ኃጢአት ባርነት ተመልሰን መውደቃችን ነው፡፡ ልባችን ከእርሱ የራቀ፣ መንፈሰ ቅዱስ እንደምን ሕይወታችን ሊሆን ይችላል?

ከጸሎተ ጋር የሚስተካከል ምንም ነገር የለም፤ ምክንያቱም የማይቻለውን እንዲቻል፣ ከባዱንም ቀላል ያደርጋልና፡፡ በጉጉት የሚጸልይ እና እግዚአብሔርን ያለመሰልቸት የሚጠራ ሰው ወደ ኃጢአት አይወድቅምና፡፡

የሚጸልዩ በእርግጥ ይድናሉ፤ የማይጸልዩ ደግሞ በእርግጥም ወደ ፈተና ይገባሉ፡፡

ጸሎትና ክርስቲያናዊ ሕይወት አይነጣጠሉም ምክንያቱም ሁለቱም የሚመለከቱት ከፍቅር የሚመነጨውን ያንኑ ፍቅርና ራስን መካድን ነው፤ ከአብ የፍቅር ዕቅድ ጋር የሚሆን የልጅነትና ፍቅርን የተላበሰ መጣጣም፣ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር ይበልጥ በሚያመሳስለን መንፈስ ቅዱስ የሚሆን ለዋጭ አንድነት እንዲሁም ኢየሱስ እኛን የወደደበት ለሰዎች ሁሉ ያለው ያው ፍቅር ነው፡፡ "በስሜ የምትለምኑት ሁሉ አብ ይሰጣችኋል፡፡ እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ይህን አዝዛችኋለሁ" ዮሐ 15፡ 16-17

ጸሎትን ከሥራ ጋር፤ መልካም ሥራንም ከጸሎት ጋር የሚያዋሕድ እርሱ "ያለማቋረጥ ይጸልያል፡፡ ያለማቋረጥ የመጸለይን መርሕ ተጨባጭ ሊሆን ይችላል ማለት የምችለው በዚህ መንገድ ብቻ ነው፡፡

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት