ቱርክ ውስጥ አንድ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲይን ጳጳስ ተገደሉ።
- Category: ዜናዎች
- Published: Friday, 04 June 2010 22:19
- Written by Super User
- Hits: 2273
- 04 Jun
Independent Catholic News -Thursday, June 3, 2010 - እስከንደሩን በምትባለው አንዲት የቱርክ ከተማ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ሉዪጂ ፓዶቨዜ (63 ዓመት ዕድሜ) በትላንትናው ዕለት በስለት ተወግተው መገደላቸው ታወቀ። በሜዲትራንያን ወደብ አጠገብ በሚገኘው የበጋ መኖሪያ ቤታቸው ጓሮ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ከአራት ዓመታት በላይ መኪና በማሽከርከር ያገለግላቸ በነበረው ሰው ጥቃቱ የተፈጸመባቸው መሆኑም ተገልጿል። የቱርክ ባለሥልጣናት ይህ ሁኔታ ጸረ ክርስቲያን ጥላቻዊ አቋምን ያለመ አይደለም ብለዋል። የቱርክ ፖሊስ ገዳዩን በእስር የያዙት ሲሆን ሰውየው ያልተረጋጋ አእምሮ ያለውና ከበድ ያለ ሥነ ልቦናዊ ችግር ውስጥ መሆኑን አሳውቀዋል።
ትውልደ ጣልያን የሆኑት አቡነ ፓዶቬዘ በአናቶሊያ የርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሐዋርያዊ እንደራሴና የቱርክ ጳጳሳት ጉባኤ ኀላፊ የነበሩ ሲሆን ከጥቃቱ በኋላ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል በመወሰድ ላይ ሳሉ ነበር ነፍሳቸው ያለፈችው። ር.ሊ.ጳ. በቆጵሮስ በሚያደርጉ ሐዋርያዊ ጉብኝት ለአጃቢነት ወደዚያው ሊያመሩ በዝግጅት ላይ ነበሩ።