እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

3. ሸማኒዝም - ቅድመ ታሪክ ምንኩስና?

3. ሸማኒዝም - ቅድመ ታሪክ ምንኩስና?

በዓለም ታሪክ ከሚታወቁ ዓበይት ሃይማኖቶች በተሟላ መልኩ ሃይማኖት ተብለው ሊጠሩ ከሚችሉት ጥንታዊና ቀዳማዊ የሚባለው ሂንዱዊዝም ነው። በምንኩስና ሕይወት ታሪክም ጥንታዊ የምንኩስና ሕይወት የሂንዱዊዝም ምንኩስና እንደሆነ ታሪክ ይመሰክራል። ነገር ግን የተዋቀረና መልክ ያለው ሃይማኖት ከመኖሩ በፊት ለሂንዱዊዝምም ሆነ ለሌሎች ጥንታውያን ሃይማኖቶች ምንኩስና መሠረት የሚሆን አንደርዳሪ እውነታ ነበረ ወይ ብለን ብንጠይቅ በቅርብ የተደረጉ ጠለቅ ያሉ የታሪክ ዳሰሳዎች - አዎን ይሉናል።

ሸማኒዝም ይባላል ይህ ቢያንስ 10,000 ዓመታት ከክ.ል.በፊት እድሜ ያለው መንፈሳዊ ልምምድ። ይህ በሰው ልጅ የታሪክ ሂደት ውስጥ ቅድመ ታሪክ ተብሎ በሚጠራበት ማኅበረሰብ ውስጥ ለተወሰነ የቤተሰብ ሐረግ የተሰጠ ልዩ ጥሪ ተብሎ የሚታሰብ ነው። ይህ ጥሪ የነበረው ሰው ለልዩ አገልግሎት ከሕዝቡ የተለየ ይሆናል - በመጽሐፍ ቅዱሳዊ አባባል በዓለም ይሆናል ግን የዓለም አይሆንም። ሸማን - ማለትም የዚህ ጥሪ ባለቤት የሆነ ሰው - በሕዝቡና በፈጣሪያቸው መካከል የመለኮታዊ ኃይል ክፍል ሆኖ የሚያገናኝ ሲሆን - ከካህናት ግን የተለይ ሚና ነበረ። አብዛኛውን ጊዜ ሸማን ለሕዝቡ የፈውስን ሚና ይጫወት ነበር።

አብዛኞቹ ሸማኖች ከማንኛውም ዓይነት ሥራ ራሳቸውን ያገለሉ ሲሆን፤ የሆነ ሙያ መሥራት ካለባቸውም ሕዝባቸው የተስማማበትና ያጸደቀው መሆን ነበረበት። በርግጥ ሸማኒዝም ማኅበራዊ ሕይወት እንደነበረው በግልፅ ታሪካዊ መረጃ ባይኖርም አኗኗራቸው ግን ማኅበራዊ ትስስር እንዳለው ግልፅ ነው። በዚህም በሰው ልጅ ውስጥ ላለው መንፈሳዊ ጥማት መልስ ለመሆን በሕዝባቸው መካከል ለሕዝባቸው ተለይተው መኖር ነበር።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት