እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ጥሪ

ጥሪ ማለት የተወሰኑ ሰዎችን ከተለመደው አናኗር ልዩ ዓይነት የሕይወት ምርጫን እንዲከተሉ የሚያደርግ የእግዚአብሔር ፈቃድን መከተል ማለት ነው። ጥሪ የተለየ ተልእኮ ወራሽ ያደረገንን ሰማያዊው አብን የማፍቀራችን መገለጫ ምልክት ነው...

ጄምስ አልበሪዮን (አባ)

የተለያዩ የመገናኛ ብዙኀን ማስታወቂያዎችን አስተውሉ፤ ወጣቶች ውስጣቸውን እንዳያዳምጡ በማድረግ ቁሳዊና ጊዜያዊ የሆኑ ነገሮች ላይ እንዲያተኩሩ ያደርጓቸዋል። የነገሮችንም ትርጉም ያዘበራርቃሉ፤ ስለዚህም 'በሕይወት ውስጥ የእኔ ሚና ምንድነው?' የሚለውን መሠረታዊ ጥያቄ ለመመለስ ለወጣቶች አዳጋች ጊዜ ሆኗል።

አንዲት ካናዳዊት ምእመን

ጥሪ ማለት በርግጥ አጭር ገለጻ ሰጥተን ማለፍ የምንችለው ጉዳይ አይደለም። በተለያየ መልኩ ቃሉን ማስገባት ስለለመድን በድፍኑም ቀላል ሃሳብ ያለው ነገር አድርገን መደምደም የለብንም። የስልክ ጥሪ፣ የሠርግ ጥሪ፣ የምርቃት ጥሪ፣ አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ፣ ሙያዊ ጥሪ፣ የምንኩስና ጥሪ፣ የክህነት ጥሪ፣ የተክሊል ጥሪ፣...የሞት ጥሪ። እነዚህና ሌሎችም መሰል አጠቃቀማችን ውስጥ በጣም የትርጉም ልዩነት ቢኖርም ጥሪ የሚለው ሃሳብ ግን ሁሌ አንድ የጋራ መልእክት አለው:- ከ...ወደ፣ ጠሪና ተጠሪን፣ ጥያቄና ምላሽን...ያመለክታል።

በዚህ ገጽ እኛ ልናነሣ የምንፈልገው ጥሪ ጊዜያዊ የሆኑ ጥሪዎችና በሞት ጥሪ ድምዳሜ የሚያገኙትን የጥሪ ዓይነቶች ሳይሆን በዚህች ምድር የሚጀመርና ሞት መሻገሪያው በመሆን ከጠሪው እግዚአብሔር ጋር የሚያስተሳስሩን ዓይነት የጸጋ ጥሪዎችን ነው። የሰው ልጅ በሙሉ ዐቢይ ጥሪ የቅድስና ጥሪ ነው። ይህም ሰው ጎደሎ ማንነቱን ከእግዚአብሔር ፍጽምና የሚሞላበት፣ ክርስቲያናዊ ሕይወቱን በእርሱ ፈቃድ መምራት ማለት ነው።

በቤተ ክርስቲያናችን ብሎም በአዲስ ኪዳን የምናገኛቸው ጥሪዎች አንድም በትዳሩ ዓለም በእግዚአብሔር እንደተሳሰሩ በመገንዘብ የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያኑ ግንኙነት ምልክት በመሆን የፍቅር፣ የትእግስትና የመቻቻል አብነት ሆኖ መኖር (ኤፌ. 5:22-ፍጻሜው) አሊያም ጌታ ራሱ ይህ ለሁሉም አልተሰጠም (ማቴ.19:12፤29 )ያለውን የድንግልና ሕይወት በመምረጥ በንጽሕና መኖር (ምንኩስና) ነው።

ሰው ሕይወቱን የጥሩ ነገሮች ሁሉ ጥሩ፣ የውብ ነገሮች ሁሉ ውብና የመጨረሻ እውነት ብሎ ላመነበት ነገር መስጠት ሲችልና የዚህም አጋዥና ፈጻሚ እግዚአብሔር መሆኑን ሲያውቅ ያ የጥሪ ሕይወት ነው። ትልቅ ነገርን ዓላማው አድርጓልና በእንደዚህ ዓይነት ሕይወቶች ውስጥ የሚነሡት ፈተናዎችም በተፈጥሯቸው ቀላል ሊሆኑ አይችሉም። ነገር ግን አሻግሮ የሚያየው ነገር ስላለ በጉዞ የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች ማዶ በሚያየው ጠሪው ኃይል ይሻገራል። ይህ እውነት የሚያስገነዝበንም ሌላ ቁምነገር ቢኖር ጥሪ አንድ ጊዜ ተጠርቻለሁ አከተመ የሚባልለት ነገር ያለመሆኑን ነው። ጠሪያችን ጋር ደርሰን ፊት ለፊት ማየት እስክንችል ድረስ ድንግዝግዝ ነው፤ ድንግዝግዝ ደግሞ በየጊዜው ማስተዋልና የተጠራንበትን አቅጣጫ ለመጠብቅ ዘወትር ዝግጁ ካልሆንን የጠሪያችንን መንገድ ሊያስተን ይችላል።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት