Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የብፁዕ አቡነ ኪዳነማርያም ጸሎተ ፍትሐት

 

የብፁዕ አቡነ ኪዳነማርያም ፀሎተ ፍትሐት ሐሙስ ግንቦት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ በ11፡30 በአዲስ አበባ ልደታ ማርያም (ካቴድራል) ቤተክርስቲያን ወዳጅ ቤተዘመዶቻቸው በተገኙበት ተከናውኗል፡፡

 

የፍትሐት ሥነስርዓቱን የመሩት ብፁዕ አቡነ ብርሃነየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሲሆኑ በሥነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት፣ ብፁዕ ሊቀጳጳሳት ጆርጅ ፓኒኩለም በኢትዮጵያ የቅድስት መንበር ተወካይ፣ ክቡር አቶ ስዩም መስፍን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ሌሎች የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተወካዮች፣ ቤተዘመዶቻቸው፣ በርካታ ካህናት፣ ደናግልና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

 

ብፁዕ ሊቀጳጳሳት ብርሃነየሱስ የብፁዕነታቸውን የህይወት ዘመን አገልግሎት የገለፁ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ተስፋሥላሴ የዓዲግራት ሀገረ ስብከት ጳጳስ ከብፁዕ ወቅዱስ ርእሰ ሊቃነጳጳሳት ቤኔዲክቶስ 16ኛ የተላከውን የሃዘን መግለጫ በንባብ አሰምተዋል፡፡

የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀብር ቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2001 ዓ.ም. በአዲግራት እንደሚፈጸም ተገልጿል፡፡

 

 

 

 

 ብፁዕ አቡነ ኪዳነ ማርያም ባደረባቸው ህመም ከሁለት ዓመታት ላላነሰ ጊዜ በአዲስ አበባና በሮማ ከተማ ህክምና ሲደረግላቸው የቆየ መሆኑ ይታወሳል፡፡ 

 

 

 

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽ/ቤት

 ማህበራዊና ህዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ

 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።