Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ ቼክ ሬፐብሊክን ይጐበኛሉ

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ የቼክ ሬፐብሊክ መንግሥት መሪ ፕሬዝዳንት ቫክላቭ ክላዉስ እና የሀገሪቱ ረኪበ ጳጳሳት ባደረጉላቸው ግብዣ መሠረት፣ እኤአ ፊታችን መስከረም ወር 26 ቀን በረፓብሊክ ቸክ ሐዋርያዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ የቫቲካን ማኅተም ክፍል መገለጫ አስታውቀዋል።

በዚሁ መግለጫ መሠረት፡ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ በረፓብሊክ ቸክ ቆይታቸው ርእሰ ከተማ ፕራግ ብርኖ ስታራ፡ በለስላቭ ይጐበኛሉ።

ይህ ቅዱስ አባታችን በነዲክቶስ በቸክ ረፓብሊክ የሚያካሄዱት ጉብኝት አሥራ ሶስተኛ አገሮች አቀፍ ሐዋርያዊ ጉብኝት መሆኑ ነው።

ነፍሰኄር ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ እኤአ በ1997 ዓ.ም ረፓብሊክ ቸክ መጐብኘታቸው የሚታወስ ነው።

ትናትና የቸክ ረፓብሊክ መንግሥት መሪ ፕረሲዳንት ቫክላቭ ክላውስ ቫቲካን የጐበኙ ሲሆን ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶ ከየቅድስት መንበር ዋና ጸሐፊ ከብፁዕ ካርዲናል ታርቺስዮ በርቶነ እና ከየውጭ ጉዳይ ዋና ተጠሪ ከሊቀ ጳጳሳት ከብፁዕ አቡነ ዶመኒክ ማምበርቲ ጋር መገናኘታቸው ይታወቃል።

የቫቲካን መግለጫ እንዳመለከተው ፡ የቸክ ረፓብሊክ ፕረሲዳንት ክላውስ ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ከየቅድስት መንበር ዋና ጸሐፊ ከብፁዕ ካርዲናል ታርቺስዮ በርቶነ እና ከሊቀ ጳጳሳት ከብፁዕ አቡነ ዶመኒክ ማምበርቲ ጋር በተገናኙበት ግዜ ፡ የቸክ ረፓብሊክ ወቅታዊ ሁኔታ፡ የሀገሪቱ መንግሥት ከካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ጋር ያላትን ግኑኝነት እና የረፓብሊክ ቸክ ክርስትያናዊ መንፈሳዊ እና ባህላዊ እሴቶች ትኩረት በሰጡ ጉዳዮች ተነጋግረዋል።

 

የቸክ ረፓብሊክ መንግሥት መሪ ፕረሲዳንት ቫክላቭ ክላውስ ከግንኘቱ በኋላ እንደገለጡት፡ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክቶስ ሀገራች እንዲጐበኙ የተደረገላቸው ዕድሜ አክብረው ፊታችን መስከረም ወር መጨረሻ ላይ ሀገሪቱ ለመጐብኘት ዝግጁ እና ደስተኛ መሆናቸው እንደገለጡላቸው እና ከፈተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ለመገናኛ ብዙኀን መግለጣቸው ተመልክተዋል።

 

 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።