እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ሁላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች በሥራችሁ አሜን በሉ! ዘልደት

እንኳን ለ2005 ብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ!
‹‹ምሕረትና አውነት ተገናኙ፣ጽድቅና ሰላም ተስማሙ፣እውነት ከምድር በቀለች ጽድቅም ከሰማይ ተመለከተች›› መዝ 85፡10-11 ይህ ትንቢት በመድኃኒታችን በአየሱስ ክርስቶስ ልደት ተፈጸመ፤ከድንግል ማርያም በተወለደው በኢየሱስ ምሕረትና እውነት ተገናኙ፤ጽድደቅና ሰላምም በሱ ተስማሙ፤እውነትም ከምድር በቀለች፤ጽድቅም ከሰማይ ወደ ምድር ተመለከተ፡፡ ይህ እውነት ምንድነው ብንል የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ምድሩ ደግሞ ሥጋው ነው፤ ክርስቶስ ከማን ተወለደ ብንል ያችን ምድር እናገኛለን፡ እሷም ምድር ንጽሕት የሆነች ቅድስት ድንገል ማርያም ናት፡፡

በዘላለማዊ አባቱ እቅፍ የነበረው የእግዚአብሔር ልጅ በናቱ እቅፍ ለመሆን ከምድር ወጣ፣ሰማየ ሰማያት ሊይዙት የማይችሉት እውነት በግርግም ለመተኛት ከምድር ወጣ፡፡ ይህንን ያደረገው ለራሱ ጥቅም ሳይሆነ ለኛ ብሎ ነው፡፡ አማኝ የሆነ ሁሉ እዚህ የእምነትን ኃይል ያያል፡ እግዚአብሔር መሆን የማይችለውን ነገር አደረገ ይኸውም ሥጋን ለበሰ፣ እኛም ከአቅማችን በላይ የሆነውን እንድንችል አደረገ፡፡ሁሉን የሚችለው ፍቅሩ የሰው ልጅ አዕምሮ ሊገምተው የማይችለውን አደረገ፤ይኸውም ለትልቅነቱ ወሰን የሌለው እሱ ሕፃን ሆኖ የሰው ልጅ ሁሉ ቤተሰብ ሆነ፡፡ ይህን ሁሉ ማድረግ የቻለ እግዚአብሔር ግን እኔ የልቤን የእምነቴን በር ካልከፈትኩለት ወደኔ ሊገባ አይችልም፤ ሰው እግዚአብሔር በሕወቱ እንዳይገባ ሊያደርግ ይችላል፣ በሕይወቱም እንዳይሠራ የማድረግ ችሎታ አለው፡፡ለመሆኑ አሁን በሕይወታችሁ እየሠራ ያለ ማነው? ምድር ፍሬዋን ሰጠች መዝ. 67፡6 ዱሮ የተረገመችው ምድር አሁን ፍሬ ሰጠች ከሰው እግዚአብሔር ተወለደ፤ በሕይወታችን ፍሬ የምንሰጥበት ጊዜ ነው፡፡ በሱ ሁላችን ፍሬ የሚሰጥ ምድር እንሆናለን፡፡እሱ የሌለው ፍሬ አልባና የተረገመ በለስ ነው፡፡(ቅ.አጎስጢኖስ፣በነዲክቶስ ረ.ሊ.ጳ)፡፡

የገና ወቅት ለእግዚአብሔር እሺ ማለትን የምንማርበት ጊዜ ነው፤ እንደቃልህ ይሁንልን ስንል የእግዚአብሔር ቃል በሕይወታችን ኀይልና ብርሃን ሆኖ በእግዚአብሔር መንግስት እንድንኖር ያደርገናል፤ የእግዚአብሔር መንግስት ልጆችም ያደርገናል፤ እስቲ በምናደርገው ሁሉ አንድ ላይ ሆነን ለእግዚአብሔር መንፈስ ተገዝተን ለሱ እሽ እንበል ክብር ለሱ ይሁን! አሜን?
በዚህ ዓለም ራስ ወዳድነት የሌለው ጥሩና መልካም ምድር አለ፤እግዚአብሔር በኛ መካከል መኖሪያው ያደረው ምድር አለ፤ የድንግል ማርያም ሥጋ የሱ ማደሪያ እንደሆነ ያንተም ያንችም ሥጋ የሱ ማደሪያ ነው፡፡ እናንተም ሕያው መኖሪያው ነችሁ፡፡ ስለዚህ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ ሥጋችንን ልንገለገል አልተፈቀደም ስለሆነም ኢሱስ በሥጋው በፈጸመው ሥራው ሁሉ እግዚአብሔርን እናዳከበረ ሁሉ እኛም በሥጋ በምንፈጽመው ሥራችን ሁሉ እግዚአብሔርን እናክብረው፡፡ እሱ ሰላማዊ ሆኖ በትሑት ሕፃን መልክ እንደተገለጸ ሁሉን ትተን ትሑታን ሆነን የሱ መንፈስ መኖሪያ ሆነን ፈለጉን እንከተል፡፡
በሰማያት ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን በምድርም በጎ ፈቃድ ላላቸው ሰዎች ሰላም ይሁን! በቃል ሳይሆን በሥራችሁ ሁላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች አሜን በሉ!

በአባ ወልደ ትንሣኤ ባለወልድ - ሲታዊ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት