እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

በሥጋ ልጇ ከመሆኑ በፊት የእምነቷ ልጅ ነው!

YeEmnet Enat(ማቴ 2፡1-12) የማርያም የእምነቷ ኀይል ኢየሱስ ከእርሷ እንዲጸነስና እንዲወለድ አደረገ፤ ስለዚህም በሥጋ ልጇ ከመሆኑ በፊት የእምነቷ ልጅ (ፍሬ) ነው፤ ሐዋርያት የሰናፍጭ ቅንጣት የምታክል እምነት እንኳን እንዳልነበራቸው ኢየሱስ ተናግሯል፤ እሷ ግን እምነቷ ሙሉ ስለሆነ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንዲወለድና ዓለምን እንዲያድን አደረገ፡፡ እሷ በእምነቷና በጸሎቷ ሰዎች በእግዚአብሔር መንግስት እንዲወለዱ የምታደርገው የቤተክርስቲያን አርአያ ናት፡፡ እሷ በእምነቷ ኃይል የኢየሱስ ክርስቶስ እናት በመሆኗ ምክንያት የኢየሱስ ክርስቶስ ለሆኑ ሁሉ በእምነት እናት ትሆናለች፡፡ ሙሉ በሙሉም ለእግዚአብሔር መገዛትን የክርስቶስ የሆኑ ሁሉ የሚማሩት ከእርሷ ነው፣ እሷ ከተዘለለች እምነታችን መሠረት እንደሌለው ቤት ይሆናል፡፡

ስለዚህ የጌታ ልደት በመጀመሪያ ደረጃ የማርያምን እምነት ሲያመለክት ቀጥሎ የቅዱስ ዮሴፍንና የእረኞችን እምነት ያመለክታል፤ የጥምቀቱ (አሰተርእዮ) ግልጸት የአይሁድን ንገሥ ለማክበር ከምዕራብ ወደ ምስራቅ የመጡትን የሰብአ ሰገልን እምነት ይገልጻል፡፡ ማርያም የተስፋውን ቃል በእምነት ሲጠባበቅ የኖረውን የእስራኤልን ሕዝብ ቅሪት ስትወክል ሰብአ ሰገል ደግሞ ሰላምን፣ እውነትን፣ ፍትሕንና ነፃነትን የሚፈልጉ ሕዝቦቸን፣ ሃይማኖቶቸን፣ ባህሎችንና ሥልጣኔዎችን ይወክላሉ፡፡{jathumbnail off}

ማርያም ለአበው በተገለጸው እግዚአብሔር የሚያምነውንና የሚያውቀውን ሕዝብ ስትወክል እምነቷም በእምነት አባታችን የሆነውን የአብርሃምን እምነት ይመስላል፡፡በአብርሃም አዲስ የተስፋ ዘመን ጀመረ፤በማርያም እምነት ደግሞ ያ ተስፋ እውን ሆኖ አዲስ የደኅንነት ዘመን ጀመረ፡፡ በዚህም ምክንያት የእምነቷ ፍሬ የሆነው የክርሰቶ ብርሃን ቅን ልቦና ላላቸው ሁሉ የተፈጥሮ ምልክትም (ከዋክብት) ሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጽ እንዲገባቸው ያደርግና ወደ እውነት እንዲመጡ ያደርጋቸዋል፤(ሰብአሰገልን ኮከብ እንደመራቸው)፡፡ የዚህ ንባብ መልእክት፤ እንደ ሰብአ ሰገል ቅን ልቦና ያላቸውና ለእውነት ክፍት የሆኑ ሁሉ እግዚአብሔርን በኢየሱስ አማካይነት ሊያውቁትና ከሱ ጋር አንድ ቤተሰብ መሆን እንደሚችሉ ማረጋገጥ ነው፡፡ ስለዚህ የክርስቶስ የሆናችሁ ሁሉ ለእውነት በቅንነት የምንገዛና እውነትን በቅንነት የምንፈልግ ከሆነ መጽሐፍ ቅዱስም ሆነ ዙሪያችንን ከበው ያሉ ነገሮች ሁሉ በክርሰቶስ ብርሃን አማካይነት ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሱን ናቸው፤ የእውነትም ፀሐይ በርቶልናልና፤ መድረሻችንም አንድያ ነው እሱም ሁላችን በኢየሱስ ትስብእት /ሰው መሆን/ አንድ ሆነን በእግዚአብሔር ቤት አንድ ቤተሰብ መሆን ነው፡፡ ይትባረክ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ አሜን፡፡

አባ ወልደ ትንሣኤ ባለወልድ - ሲታዊ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት