እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የእግዚአብሔርን ቃል የሚያዳምጥ ጆሮ - ቅድስት ቤተሰብ -ዘጥምቀት ፪ኛ

ሉቃ 2፡41-52 (ዘጥምቀት አስተርእዮ 2ኛ)

እዚህ ወንጌሉ ሊያስተምረን የፈለገው ነገር ክርስቲያን ተብለን ልንጠራ የምንችለው በቤተሰባችን እያንዳንዳችን ለእግዚአብሔር ዕቅድ/ ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጥ ሕይወት ስንኖር መሆኑን ነው፤በዚሁ ወንጌል በዚህ በቅድስት ቤተሰብ እናት ሆና የምናገኛት ማርያም የእግዚአብሔርን ቃል የምታዳምጥ ሴት ሆና እናገኛታለን፤እግዚአብሔር ዓለምን ለማዳን ባለው ዕቅድ የዘመኑ ፍጻሜ ሲደርስ ለማርያም ቃሉን ይናገራል፤እሷም ምንም እንኳን ያ ቃል ለመረዳት የሚያስቸግር መስሎ ቢታያትም ‹‹እነሆኝ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› በማለት ተቀበለችው (ሉቃ 1፡39-45)፡፡ በዚሁ ቤተሰብ አባት የሆነው ዮሴፍም እንዲሁ የእግዚአብሔርን ቃል የሚያዳምጥ ጆሮ ያለው ሰው ሆኖ እናገኘዋለን እግዚአብሔርም በመልአኩ በኩል የተናገረውን ቃል ሰምቶ በፍጹም ልቡ ይታዘዛል (ማቴ 1፡24)፡፡እንዲሁም በዚሁ ቤተሰብ ልጅ የሆነው ኢየሱስ የእግዚአብሔር መገለጫ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ እንግዲህ በዚህ ቤተሰብ እያንዳንዳቸው ለእግዚአብሔር ፈቃድና ዕቅድ ቅድሚያ በመስጠት ይኖራሉ፤የእግዚአብሔርንም ቃል መስማትና በሱም መመራት እግዚአብሔርም በሕይወታቸው በነፃነት እንዲገለጽ ያደርጋሉ፡፡ክርስቲያን የሆነ ቤተሰብም እንዲሁ በተመሳሳይ መልኩ የእግዚአብሔርን ቃል፡ ሕይወቱን የሚመራ ቀዳሚ መንገዱ/ሐሳቡ ሊያደርገው ይገባል፡፡

ክርስቲያን ቤተሰብ በየመደቡ (አባት፣እናት፣ልጅ) የሕይወቱን ራእይ፣ዓላማና ዕቅድ እግዚአብሔር በቃሉ እንዲመራውና እንዲገለጽበት ሊፈቅድ ይገባል፡፡ ከክርስቲያንም ቤተሰብ የሚጠበቀው የያንዳንዱ አባል ሕይወት በእግዚአብሔር መንፈስ የተሞላ ሆኖ እርስ በርሳቸውም ሆነ ከሌሎች ሰዎች ጋር በምሕረት፣ በትዕግስት፣በትሕትናና በየዋህነት በፍቅርም የተሞላ ግንኙነት እንዲሆራቸው ነው፡ቆላ 3፡11-15፡፡ እኛም በየቤተሰባችን እንደ ማርያም ዮሴፍና ኢየሱስ ለእግዚአብሔር ጉዳይ ቅድሚያ የምንሰጥ ከሆነ ትልቁ ቤተሰባችን ማለትም የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተክርስቲያን በሰላምና በቅድስና በፍቅርም የተመሠረተ ሕይወት ይኖራታል፡፡ ስለዚህም በየቀኑ በተለያዩ መንገዶች ለያንዳንዱ ቤተሰብ አባል የሚመጣውን ፈተናና ዕንቅፋት በቤተሰባችን እንዲገዛ በተቀበልነው/በፈቀድነው በእግዚአብሔር ኃይል እየተቃወምንና እየተዋጋን የቅድስት ቤተሰብን አርአያ ተከትለን ለእግዚአብሔር የመታዘዝ ሕይወት እንድንኖር ተጠርተናል፡፡የቅድስት ቤተሰብን አብነት መከተል ቅዱሳን ያደርገናል፤ይህም የቅድስና ሕይወት (እግዚአብሔርን የመስማትና የመታዘዝ ሕይወት) ትንሹም ሆነ ትልቁ ቤተሰባችን እንዳይፈርስ የሚያደርግ ኃይልና መከላከያም ነው፡፡ እንግዲህ የክርስቶስ አካል የሆንን ሁላችን የእግዚአብሔር ፈቃድ በወለደንና ባዛመደን ቤተሰብ ሁሉ ለሱ በመገዛት ሰላማችን የሆነውን የክርስቶስን ሰላማዊ ሕይወት እንኑር ሮሜ 5፡1-2፡፡

ይትባረክ ኢየሱስ ክርስቶስ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት