እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

የጾም ታሪካዊ አመጣጥ

የጾም ታሪካዊ አመጣጥ

የጾምን ታሪካዊ አመጣጥ ስንመለከት ደግሞ በመጀመሪያዎቹ ክፍለ ዘመናት ተጀምሮ በቋሚነት የረቡዕና የዓር ጾም ክርስቲያኖች ይጾሙ ነበር (ዲድስቅሊያ)።

በክርስትና ታሪክ የቤተክርስቲያንየጾም ሥርዓት (ልማድ) እንደየአካባቢው የተለያየ ባህልና አመለካከት ይዞ የመጣ ቢሆንም የጌታን ስቅለትና ሞት ለማስታወስ ሲባል በምዕራቡም ሆነ በምሥራቁ ዓለም የዓርብ ጾም ይተገበር ነበር።

በምዕራቡ ዓለም ወደ 400 ዓ.ም. አካባቢ አረቡዕ ዕርብ ጾም በቅዳሜ ጾም እንደተተካ ታሪክ ሲያስረዳ  የዐቢይ ጾምን ጨምሮ የታላላቅ በዓላት ዋዜማዎች በጾም ማሳለፍ ደግሞ ከጥንት ጀምሮ የመጣ ልምድ ነው። እናም የእስራኤላውያን ልማድን በመከተል ክርስቲያኖች ጾምን ይጾሙ የነበረው ከሁሉም የምግብ ዓይነት ጸሐይ እስከትጠልቅ ድረስ በመከልከ እና በማታ ጸሎት በማሳረግ ነበር።

በ9ኛው ክ.ዘ. የነበረውን የጾም አተገባበር ስንመለከት ደግሞ በሁሉም ክርስቲያን አገሮች እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ከምግብና ከውሃታቅበው በምዋል ነበር። ሆኖም ግን ከዕለት ሥራው ብዛት የተነሣ ሳይበሉ እስከዚያ ሰዓት ድረስ መቆየት ለብዙዎች አስቸጋሪ እንደነበር ግልጽ ነው።

በገዳማትም ቢሆን የነበሩት የጾምና ይተጋድሎ ጊዜያት በርከት ያሉ ሆነው በገዳማት ሕግና ቤ/ያን ሕግጋት የተቀመጡ አጽዋማት ይተገበሩ ነበር። በገዳሙ ትእዛዝ ብቻ ይየሚጾሙ ጾሞች በሚደረጉበት ዕለት በማታ ትንሽ መክሰስ ዳቦና የወይን ጠጅ እንዲቀምሱ ይፈቀድላቸው ነበር።

በምሥራቃዊቷ ቤ/ያን ያለውን የጾም ታሪካዊ አመጣጥ ስንመለከት ደግሞ ከመጀመሪያው ክ.ዘ. ጀምሮ ረቡዕና ዓርብ በግሪክ ቤ/ያን ምንም ዓይነት ምግብ አይበላበትም ነበር። ከጊዜ በኋላ ሌሎች ቀናቶችና ወቅቶች ተጨመሩ። የሁዳዴ ጾም የተጀምረው ከ2ኛው ክ.ዘ. ጀምሮ ነው። 4ኛው ክ.ዘ. ላይ ስለ የተቀደሱ 40 ቀናት ይነገር ነበር። ከዚሁ ከታላቁ (ዐቢይ) ጾም በተጨማሪ ሌሎች 3 የጾም ጊዜያት በምሥራቁ ዓለም ተለምደው ነበር። እነዚህም፦

  1. የሐዋርያት ጾም የሚባለው (ሰኔ ወር ውስጥ 2 ቀናት)
  2. የማርያም ጾም (ነሐሴ 1-14)
  3. የገና ጾም (ኅዳር 15-ታኅሣሥ 24) እ.ኤ.አ.

እነዚሁ 3ቱ ንኡሳን አጽዋማት እስከ 8ኛው ክ.ዘ. ግዴታዊ አልነበሩም። በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት የአጾም ቀናት በተለያዩ ምክንያቶች እየተበራከቱ መጡ። እንዲያውም በግሪክ ቤ/ያን እስከ 180 ቀናት ያህል በዓመት ውስጥ ይጾም ነበር። የግብጽ መነኮሳት እንደ አባ እንጦንዮስ ጽምን ያሳልፉ የነበረው ትንሽ ዳቦ በውሃና በጨው በመመገብ ብቻ ነበር በምሥራቁ ዓለም ጾም በኣም በታላቅ ተጋድሎ ይጾም ነበር። በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ዛሬም ድረስ ቆሎን በደረቅ ምግብ ብቻ እየተመገቡ የማሳለፍ ልማድ ይታያል።

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት