እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ሚያዚያ 21ቀን /2004 ዓ.ም - ከማመን ልባቹህ የዘገየ.....

ሚያዚያ 21ቀን /2004 ዓ.ም - ከማመን ልባቹህ የዘገየ.....

2ቆሮ 5፡11-21 ጴጥ 3 ፡14-18 ሉቃ 24፡13-35

መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር በሕይወት ያሉ ሁሉ ስለ እነርሱ የሞተው እና ከሞትም ለተነሳው እንዲኖሩ እንጂ ከእንግዲህ ወዲህ ለራሳቸው ሲሉ እንዳይኖሩ ክርስቶስ ለሁሉም ሞተ ይላል፡፡(2ቆር 5፡15)ቅዱስ ጳውሎስ ራሱን ጨምሮ ክርስቶስ ሰለ ሰው ልጅ ፍቅር በመስቀል ላይ እንደሞተ ያውቅ ነበር፡፡በመንፈስ ሙታን የሆኑ ሰዎች ሕያው ሊሆኑ የሚችሉ በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ በማመን ብቻ ነው፡፡ምንም እንኳን ይህ መልዕክት የሞኝ ተረት ቢመስልም ለሰው ልጆች ብቸኛው ተስፋ ነው፡፡ቅዱስ ጳውሎስ በድፍረት መስበኩን የቀጠለው ሥለዚህ ተስፋ ሲል ነው፡፡ እርሱ ሰዎችን የተመለከተው በሥጋ ዐይኑ አማካኝነት በጎሳቸው፣በቋንቋቸው፣በኢኮኖሚ ደረጃቸው አልነበረም ነገር ግን ጳውሎስ ሰዎችን የተመለከተው በክርስቶስ ወንጌል አማካኝነት አዲስ ፍጥረት ከመሆናቸው ወይም ለወንጌል ካላቸው የደነደነ ልብ አሮጌ ፍጥረት ከመሆናቸው አንፃር ብቻ ነው፡፡ አንድ ግለሰብ በእግዚአብሔር (በአብ ፣በወልድ፣በመንፈስ ቅዱስ )በማመኑ በውስጡ የተለወጠ አዲስ ፍጥረት ይሆናል፣አስተሳሰቡና አሰራሩ ሁሉ ይለወጣል፡፡ለዚህ ወንጌል ወደ ኤማሁስ ሲጓዙ የነበሩ ደቀመዛሙርት ምስኪን ደሃ መስሎ ከቀረባቸው ከክርስቶስ ጋር እንደተገናኙ እናያለን፡፡እነርሱም ክርስቶስን ካገኙት እና በመዓድ አብሮአቸው ከተቀመጠ በኋላ ያገኙትን ደስታ ለመመስከር ተቻኩለው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዱ፡፡የሰሙት የምስራች ቃል በእነርሱ ብቻ ተወስኖ እንዲቀር አልፈለጉም ይልቁንም ከወንድሞቻቸው ጋር ለመካፈል ወጡ፡፡ ክርስቶስም ማንንም አያስገድድም፤በፍቅርና በቅን ልብ ለሚፈልጉት ግን ራሳቸውን እስከሰጡት ድረስ ራሱን በሙላት ይገልፃል፡፡እነዚህ ሁለቱ ደቀመዛሙርት የተለያዩ ሦስት የዘመናችንን ሰዎች ይወክላሉ፤እነርሱም

1ኛ ያለ ኢየሱስ የሚጓዙ ሰዎችን

2ኛ ከኢየሱስም ጋር ቢጓዙም ማን መሆኑን የማያውቁ በደመነፍስ የሚመሩ ሰዎች

3ኛ ከክርስቶስ ጋር በኅብረት እና በትብብር በመጓዝ ፍቃደኛ የሆኑ ሰዎችን፡፡

ምንባቡስለምንይናገራል?

ከምንባቡከተሰጠንሦሥትምሳሌዎችራሳችንንየቱጋእንመድበዋለን?

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት