እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ሚያዚያ 14ቀን /2004 ዓ.ም - "ሰላም ለእናንተ ይሁን"

ሚያዚያ 14ቀን /2004 ዓ.ም - "ሰላም ለእናንተ ይሁን"

1ቆሮ 15፡1-19 1ዮሐ 1 ፡1-10 ዮሐ 20፡19-31

የእግዚአሔር ቃል ሲናገር ሐዋርያት የአይሁድ ባለስልጣናትን በመፍራት በራቸውን ዘግተው ሳለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ወደተሰበሰቡበት ቤት ገባ፡፡በመካከላቸው ቆሞ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" አላቸው፡፡በዚህ ቀን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀመዛሙርቱ ታላቁን የሰላም ስጦታ ሰጣቸው ይህ ሰላም ከሰው ልጆች ማስተዋል የሆነ እና ቅዱስ ጳውሎስ በመለኮታዊ ጸጋ ተነሳስቶ የሰበከው ነው፡፡ክርስቶስ ወደ ዓለምመጥቶ ያበሰረውን የምስራች ቀጥለው እንዲሰብኩ የስብከተ ወንጌልን ስልጣን እና አገልግሎት ለሐዋርያቶቹ ሰጣቸው፡፡በዚህም ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ መልዕክተኞች መሆናቸው ነው፡፡

ሁለተኛው ሐሳብ ስለ ተልዕኮ ጉዳይ ነው፡፡ይህም ኢየሱስ መለኮታዊ ክብሩን ሁሉ ትቶ አገልጋይ መሆኑን እንደወደደ ሁሉ የዚህ ወንጌል አገልጋዮች የእርሱን አብነት በመከተል የዚህ ዓለም ምኞት ፣ደስታ፤ ምቾትና የተመቻቸውን ሕይወት በመተው ራሳቸውን ለዘህ የወንጌል አገልግሎት መስዋዕት አድርገው ማቅረብ ማለት ነው፡፡

በሦስተኛ ትኩረት የተሰጠው ሐሳብ "መሄድ" የሚለው ነው፡፡ ወዴት እንደሚልካቸው አልገለፀም፡፡ስለዚህ እርሱ ወደፈቀደው ቦታ እንጂ ራሳቸው ወደፈለጉበት አይሄዱም፡፡እነዚህ አገልጋዮች ወደተለያዩ ሥፍራዎች ፣ወደተለያዩ ባህሎች፣ቋንቋዎች ፣የአኗኗር ዘዬዎች በመሄድ መልካሙን ዜና ያበስራሉ፡፡በመቀጠልም የኃጥያት ይቅርታን በመስጠት ከአምላካቸው ጋር አንድ እንዲሆኑ አድርጓቸው፡፡በመሆኑም ሰዎች በእግዚአብሔር ቃል ልባቸውን ሲያመቻቹ ኃጥያታቸው በትሁት ንሰሐ አማካኝነት ይቅር ይባላል፡፡ቤተክርስቲያንም ምዕመናን ከኃጥያት እንዲላቀቁ የመምከር፣የማስተማር እና ከኃጥያት የመመለስ ስራ ትሰራለች፡፡(2ጢሞ 4፡2)

ጥፋትን ቸል አትበል፣በአስጊ ሁኔታ ውስጥ ያለውንም አስጠንቅቅ፡፡ሰዎች ራሳቸውን ሲያታልሉ ዝም ብለህ አትያቸው፡፡የሰው ልጅ ሁሉ አስርቱን ትዕዛዛት በልቡ ይጠብቅ ዘንድ አስተምራቸው፤ሲበድሉት እያየህ ዝም አትበል፡፡እንዲህ ያለውን ቅዱስ ትዕዛዝ በልቡ ይጠብቅ የሚበድሉ ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርስም፡፡(ገላ5፡21ን ተመልከቱ)ተገቢው መድኅን ሁሉ ከተሞከረ በኋላ ሰዎች በኃጥያታቸው ከጸኑ በእግዚአብሔር ቃል መሰረት በሰማይ ፍርድ ይጠብቃቸዋል፡፡

ምንባቡስለምንይናገራል?

ቤተክርስቲያን የማስተማር ስራ ላይ ምን ያህል ትካፈላለህ ?

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት