እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ቃል ሥጋ ሆነ በእኛም አደረ

ቃል ሥጋ ሆነ በእኛም አደረ

የአዳም ልጆች በሙሉ እዲመጣላቸው በናፍቆት ይጠብቁት የነበረው መሲሕ የተወሰነው ጊዜ ሲደርስ መጣ፡፡ በዚህም ሁኔታ የነቢያት ትንቢት ተፈጸመ፣ ሐቅነቱ በግዙፍ በዓይን ታየ፡፡ እግዚአብሔር ለአባታችን አዳም “አዳኝ እልክልሃለሁ” እያለ አስቀድሞ ሰጥቶት የነበረው የተስፋ ቃል ዛሬ ተግባራዊ ሆኖ በዐይን ምስክር ታይቶአል፡፡ ጊዜው ከደረሰ በኋላ እግዚአብሔር በኦሪት ሕግ ሥር የነበሩትን ለማዳንና ልጆችም እንዲሆኑ መብትን ሊሰጣቸው ከሴት የሚወለድ በሕግም የሚመላለስ ልጁን ላከ፡፡ የመድኃኒታችንና የአምላካችን ደግነትና ሰውነት በይፋ ተገለጠ፡፡ ባደረግነው የጽድቅ ፍሬ ሳይሆን በምሕረቱ አዳነን፤ አምላክ እኛን ለመምሰል እንደ እኛ ምስኪን ድኻ ሰው ሆነ፡፡

በዛሬው ቀን ክርስቶስ አምላካችንም እኛን ለማዳን ተከታዮቹና ወዳጆቹ ሊያደርገን ሥጋችንን ለብሶ እኛንም መስሎ በመካከላችን መጣ፡፡ “ቃል ሥጋ ኮነ ወኃደረ ላዕሌነ - ቃል ሥጋ ሆነ በኛም አደረ”  ይላል ቅዱስ ዮሐንስ 1:14፡፡ አምላክ  ሥነ- ማዕረጉን ሁሉ ትቶ፣ ትልቅነቱን ንቆ ዝቅተኛና ደካማ ባሕርያችንን ተሸከመ፣ የራሱም አደረገው፡፡ በዚህ ጭንቅ የተሞላበት ከባድ ኑሯችን ከኃጢአት በስተቀር ልክ እንደ እኛ እንደ አንዱ ሆኖ ለመኖር ስለ ደኅንነታችን ፍቅር ከሰማይ ወደ ጊዜያዊ መኖሪያችን ወደ ምድር ወረደ፡፡

“ኦ! ፍቅር ዘጠነዝ ፍቀር ኦ! ትሕትና ዘመጠነዝ ትሕተና። ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት -ኦ! ይህን የሚያህል  ፍቅር ምን ያህል ፍቅር ነው፤ ኦ! ይህን የሚያህል ትህትናስ ምን ዓይነት ትሕትና ነው! ፍቅር ኀያሉን ወልድ  ከመንበሩ ስቦ እስከ ሞት አደረሰው”

እያለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይናገራል፡፡

ዓለም ሳይፈጠር ጀምሮ ከእርሱ ጋር በነበረ በአምላክ አንድ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ፡፡ በእውነት ብርሃን ከብርሃን እውነተኛ አምላክ ከእውነተኛ አምላክ የተወለደ እንጂ የተፈጠረ አይደለም፡፡ መለኮታዊነቱ ከአብ ጋር እኩል ነው፡፡ ሁሉ በእርሱ የሆነ ያለእርሱ ምንም የሌለ ስለ ደኅንነታችን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡

ይህ በፊታችን ያለው ትናንት የተወለደ ሰማያዊ ሕፃን ነው፡፡ ፈጣሪ ሆኖ ሳለ እኛን ለማጽናናትና የድኀንነትን ብርሃን ሊሰጠን ሕፃን ሆኖ ወደ እኛ መጣ፡፡ አዳም በልጆቹ አማካይነት ይህን መሢሕ በብዙ ምኞትና ናፍቆት ጠበቀው፤ ቶሎ መጥቶ ከመጥፎ ኑሮው እንዲያድነውም በሙሉ ልብ ተማጠነው፡፡ ቀንም ሌሊትም  ለመነው፡፡ ይኸው ዛሬ ምኞቱን ሊያሟላለት የድኀንነትን ብርሃን ሊያበራለት መሢሕ ወደ እርሱ ቀረበ፡፡ “ደስታዬ ከሰው ልጆች ጋር መሆን ነው” እያለ ከእኛ ጋር ሊቀመጥ ፈለገ፡፡ ከእኛ ጋር በመሆን ሊጠብቀን፣ በሚያስፈልገን ሁሉ ሊረዳን፣ ከጠላት ሊታደገን የምድራዊ የሰው ልጅ መልክ ለብሶ መጣ፡፡ በጸጋዎቹ ሀብታሞች ሊያደርገን የእግዚብሔርን መንገድ ሊመራን ወስኖ ከእኛ ጋር ለመኖር መጣ፡፡

ወልድ ሰው ሆነ በመካከላችንም ደግሞ ተቀመጠ፡፡ ልዑል አምላክ ስለፍቅራችን እኛን መሰለ፤ በፍቅሩና በትሕትናው እያመሰገንነው በክፋታችን ከእኛ እንዲርቅ እንዳናደርገው እንጠንቀቅ፡፡ ልባችንን ከልቡ ጋር ፈቃዳችንን ከፈቃዱ ጋረ እንድናደርገው ቃሉን እንስማ፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ እርሱን እንፈልግ፣ ኑሯችንም ከእርሱ ጋር ይሁን፡፡

ምንጭ፡

መንፈሳዊ ማሳሰቢያ

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት