እግዚአብሔር ቁጡ አይደለም
- Category: የተለያዩ አስተንትኖዎችና አስተምህሮዎች
- Published: Wednesday, 18 May 2011 06:59
- Written by Super User
- Hits: 2064
- 18 May
እግዚአብሔር ቁጡ አይደለም
የእኛ እግዚአብሔር እኛ ከምናስበው እጅግ የተለየ ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍትሕ ስለሆነ ለበደልነው ሁሉ ካሳ እንደሚፈልግ ብዙ ጊዜ ሰምተናል፡፡ ነገር ግን የእኛ እግዚአብሔር ፍትሕ ብቻ ሳይሆን ፍቅርም ነው!
እግዚአብሔርን ከእኛ ጋር ማስታረቅ አያስፈልገንም፡፡ ምክንያቱም እርሱ ራሱ እርቅ እና ይቅርታ ነውና፡፡ እኛ ነን ፊታችንን ከእግዚአብሔር የምናዞረው እንጂእግዚአብሔርማ እይታውን ከእኛ ላይ በፍጹም አንስቶ አያውቅም፡፡ እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንድንመለስ እየጠበቀን ነው፣ እንዲያውም እኛን ለመገናኘት ወደ እኛ እየሮጠ መሆኑን ልንክዳቸው የማይቻለን ጠንካራ የፍቅር ማስረጃዎቹ ይመሰክራሉ፡፡
እኛ አይደለንም የእግዚአብሔርን ቁጣ የምናስታግሰው፣ እግዚአብሔር አልተቆጣንምና ነው፡፡ ፍቅር አይበሳጭም(1ኛ ቆሮ 13፡5)፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር ነው የሰው ልጅን ቁጣ ለማብረድ የሚጥረው፡፡ ነገር ግን ይህንን ማሳካት አልቻለም ምክንያቱም የሰው ልጅ አሁንም በእግዚአብሔር ላይ እንደተቆጣ ነውና፡፡ በዘመናችን ሰብዓዊ ተፈጥሮ በእግዚአብሔር ላይ እንደአሁኑ ከፍቶ ያውቃልን? ከዚህ በፊት ባልታየ መልኩ እግዚአብሔር እየተወቀሰ ይገኛል፤ይህንን ያህል ክፉ ነገር እንዲከሰት የሚፈቅድ እርሱ ምን ዓይነት እግዚአብሔር ነው?
አብዛኛው በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ የሰው ልጅ አመጽ እውነታው ሲታይ የሚያመለክተው እኛ የምንስለውን እግዚአብሔር ባህርይ ማለትም፡- ክስ የሚመሰርት እግዚአብሔርና ለመቅጣት ጥሩ አጋጣሚ የሚጠባበቅ አምላክን ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ እግዚአብሔር ግን የሚፈራና የሚጠላ ነው፡፡ ያለ ምንም ተቃውሞ በመስቀል ላይ የተሰቀለውና እጆቹ ሁሉንም ለማቀፍ በሰፊው የተዘረጉት አምላክ፣ ሰዎችን ሁሉ ከእርሱ ጋር እንዲሁም እርስ በእርሳቸው አንድ ለማድረግ በብርቱ ይተጋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ እግዚአብሔር ደግሞ ለማፍቀር አይከብድም /አያስቸግርም!!/
ምንጭ፡ This is the day the Lord has made, 365 daily meditations: By Wilfrid Stinissen)
አባ ተሻለ ንማኒ - ሲታዊ