እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ሚያዚያ 28ቀን /2004 ዓ.ም - እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው

ሚያዚያ 28ቀን /2004 ዓ.ም - እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው

ቆላ 3፡5-17 1ጴጥ 3 ፡15-22 ሉቃ 24፡36-49

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀመዛሙርቱ እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው፡፡ እነዚህ እግሮቹ እና እጆቹ በመስቀለ ላይ ተቸንክረው ነበር፡፡ እርሱም ለዘለዓለም የማይጠፋ ምልክት እና መድኃኒት ነው፡፡ ኢየሱስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳ መሆኑን ያምኑ ዘንድ የትንሳኤው አካል መሆኑን እጁንና እግሩን ካሳያቸው በኋላ በፊታቸው ምግብ በመብላት ማንነቱን ገለጸላቸው፡፡ እነርሱም ፍጹም በሆነ እምነት አመኑ፡፡ የክርስቶስ ትንሳኤ ለእርሱ በማመን ያንቀላፉት ሁሉ በመጨረሻ የሚሱበት ምልክት ነው፤ ከትንሳኤ በኋላ የአዳኛችን ፊት አነጋገር ባሕርይ ሁሉ ከመሞቱ አስቀድሞ ሐዋርያቱ ያውቁት እንደነበረው አልነበረም፡፡ ከሞት በኋላ እንለመጣለን፡፡ ክርስቶስ ከሞት እንደተነሳ እንዲሁ እርሱን የሚያምኑት ሁሉ ይድናሉ ከሞትም ይነሳሉ፡፡ ሰዎች ከሞት በኋላ በሚመጣው ሕይወት የሰው ልጅ መልክ ምን እንደሚመስል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶናል ሰውነታቸው መንፈሳዊ አካል ተላብሶ እንለወጣለን፡፡ በመቀጠልም ክርስቶስ መከራ ይበቀላል፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሳል በስሙም ንስሐ እና የኃጥያት ሥርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል፡፡ ጌታ ራሱ ስለእኛ ሞት ተነስቷል በሕይወታችን የወደቀብንን የመቃብር ድንጋይ ማንከባለል እንችል ዘንድ እርሱ ራሱ ይረዳናል፡፡ በእርሱ ዘንድ በንስሐ ሙሉ ስርየት ኃጢአት ማግኘት እንችል ዘንድ ሞቷል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ለዓለም የሞትኩ ነኝ ዓለምም በእኔ ዘንድ የሞተች ናት" ይላል፡፡ ሐዋርያው ይህንን ቃል የተናገረው የዓለምን ነገር በምንም መልኩ የለሁበትም ማለቱ ሳይሆን ኃጥያትን ላለመስራት ቁርጥ ፍቃድ አድርጌአለሁ ማለቱ ነው፡፡

እኛም በዚህ ዓለም እስካለን ድረስ በኃጥያታችን እየተጸጸትን በትህትና ወደ እግዚአብሔር እንሩጥ፡፡ በቁጥር 51 ላይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለ4ዐ ቀናት ያህል ለደቀመዛሙርቱ ከታየ በኋላ እንዲሁ ሁሉም በዐይናቸው እያዩት ወደ ሰማይ ወጣ፡፡ ነገር ግን በደቀመዛሙርቱ ሕይወት ውስጥ መሥርቱን እንደሚቀጥል ሐዋርያት ሥራ ይናገራል፡፡ ይሁንና አንድ ቀን ምጽዓት እንዳለም ተናግሯል፡፡ ዕርገቱ ለሐዋርያት ብቻ ሳይሆን ለአዳም ልጆች ሁሉ ትልቅ ጸጋ ሆኗል፡፡ ወደ ሰማይ በወጣ ጊዜ በአዳም ኃጢያት ተዘግቶ የነበረውን የመንግስተ ሰማይ በር ከፍቶታል፡፡

ምንባቡ ስለምን ይናገራል?

በእየሩሳሌም ጀምሮ የተሰበከው ቃል ለኛ ምን ይህል ተሰብኳል?

እንዲሰበክስ ምንያደረግነው ነገር አልን?

የፊታችን ግንቦት አንድ ቀን የእናታችንን የድንግል ማርያምን የልደት በዓል እናከብራለን ና በረከተቷና አማላጅነቷ ከሁላችን ጋር ይሁን !

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት