እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ግንቦት 5 2ዐዐ4 - መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉት

ግንቦት 5 2ዐዐ4 - መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉት

ሮሜ 4፡13-24  ራዕይ 2ዐ፡ 1-6 እና 11-15    ዮሐ 21፡ 1-41

ምህረት አምላክ የእግዚአብሔር የአዳኛችን የኢየሱስ ክርስቶስ በፀጋው የሚመራን የመንፈስ ቅዱስ ሰላም እና ጥበቃ ይብዛልን፡፡እግዚአብሔር ለአብርሃም ታላቅ ነገርን ያደረገለት በእርሱ ላይ ባለዉ እምነት ነዉ፡፡ ያም የገባለትን ቃልኪዳን ለመፈጸም የመሲሑን መምጣት በተስፋ መጠበቅ ያስፈልገውም ነበር፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን የሚችል አምላክ እንደሆነ በይስሐቅ መወለድ ማየት እንችላለን፡፡ዘፍ 17፡ 17-18 አብርሐም ከነበረዉ ችግሩ ይልቅ እግዚአብሔርና የተሰጠዉን ተስፋ ይመለከታል፡፡ የአብርሐም እምነት በይገባኛል የተሞላ ሳይሆን በተስፋ ሰጪዉ አምላክ ክብርን በመስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ሺ ዓመት መጨረሻ የሌለዉ ንግስና ያመለክታል፡፡ የክርስቶስን ዘላለማዊ ንጉስነት እንድንመለከተዉ ይጋብዘናል፡፡ በወንጌሉ ሐዋርያት የሰጣቸዉን የተስፋ ቃል በመዘንጋት ተስፋ ቆርጠዉ ወደነበሩበት ታሪካቸዉ መመለሳቸዉን እና ዳግም ክርስቶስ በህይወታቸዉ ተገልጦ ‹‹ ጌታ እኮ ነዉ›› በማለት አይነ ልቦናቸዉ እንደተገለጠ በቃሉ እናገኛለን፡፡

1. ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል የሚያስተምረን በእኛ የጊዜ ቀመር ሳይሆን እንደፈቃዱ በታሪካችን ዉስጥ ያልነበረንን፡ ተስፋ የቆረጥንበትን በመፈፀም ታላቅ ነገርን በህይወታችን የሚያደርግ አምላክ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡

2. ክርስቶስ አምላካችን ፍጹም አምላክ እንደሆነ ንግስናዉም መጨረሻ የሌለዉ ልዑል የሆነ አልፋ ኦሜጋ እንደሆነ መገንዘብ ይጠበቅብናል፡፡

3. አይነ ልቦናችንን ከፍተን በቃሉ በመኖር ተስፋችንን ማለምለም ያስፈልጋል፡፡

ስለዚህ በእምነት መጽናት ፤በተስፋዉ ቃል መኖር እራሳችንን ኑሯችንን ለእርሱ መስጠት ስንችል እግዚአብሔር በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ታሪካችን ይገባል፡፡ ታላቅ ነገርን ያደርግልናል፡፡ በረከትና ዋጋዉን ያበዛል፣ ዘመናችን ልክ እንደ አብርሃም ይባረካል፡፡የበረከት አምላክ የበረከቱ ተካፈይ ያድርገን አሜን፡፡

• ምንባቡ ስለምን ይናገራል ?

• እኛስ ዘመናችንን እንዴት እናየዋለን ?

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት