እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ግንቦት 12 ቀን /2004 ዓ.ም - "ከነዚህ ይልቅ ትወደኛለህ?"

ግንቦት 12 ቀን /2004 ዓ.ም -  "ከነዚህ ይልቅ ትወደኛለህ?"

ሮሜ 6፡1-14 1ጴጥ 4 ፡1-11 ዮሐ 21፡12-25

የምህረት አምላክ የእግዚአብሔር የአዳኛችን የኢየሱስ ክርስቶስ በፀጋው የሚመራን የመንፈስ ቅዱስ ሰላም እና ጥበቃ ይብዛልን፡፡ከዚህ ከጳዉሎስ መልዕክት የምንረዳዉ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐጢያት ነፃ በማዉጣት ክፉን በማሸንፍ፣ ሕይወት የሰጠ እርሱ ነዉ፡፡በመንፈስ ቅዱስ ህይወት እንድናገኝ ሙሉ እምነት እንዲኖረን ያስፈልጋል፡፤ምንባቦች እንድናስብ ይጋብዘናል፡፡ ከክርስቶስ ጋር ያለን ህብረት ያመለክተናል፡፡ ጥምቀት የኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ተካፋይ እንደሆንንና በትንሳኤዉም ተካፋይ መሆናችንን ያመለክታል፡፡ ሐዋርያዉ ጴጥሮስ እንደ ስጋ ፍቃዳችን ሳይሆን በእግዚአብሔር ፍቃድ ዉስጥ እንድንመላለስ ይጋብዘናል፡፡ህብረታችን ፣ኑሯችን፣ ሁለንተናችንን ህይወትን በሰጠን በክርስቶስ ኢየሱስ እንዲመራ እና መገዛታችን ለክፋት እንዳይሆን ያስገነዝበናል፡፡በዮሐ. 21-15 ጀምሮ የእግዚአብሔርን ቃል ስናነብ ጴጥሮስ በክርሰቶስ ኢየሱስ የወንጌል አምባሳደር ሆኖ ሲገኝም እንመለከታለን፡፡በክርስትና ህይወት ዉስጥ ክርስቶስ ህይወታችንን እንድንፈትሽ ይጋብዘናል፡፡ እንድንታመን የእሱ አገልጋይ እንድንሆንም እንጋበዛለን፡፡ ጴጥሮስ የቱንም ያህል ደካማ ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ ግን ሀላፊነት ተሰጠዉ መንጋን የመጠበቅ፡፡ስለዚህ ከዚህ ቃል የምንረዳዉ ክፋትን በእረሱ በመታመን በማሸነፍ ፍቃዳችንን ለእርሱ በማስገዛት በእምነት ፀንተን ለሌሎች ምስክሮቹ እንድንሆን እንጋበዛለን፡፡እንዲሁም የእግ/ርን መመልከት በእርሱም ፍቃድ መመላለስ ለቅድስና የተጠራንበትን ህይወት እንድንኖር ብርታት ይሆነናል፡፡በመጨረሻ ቃሉን ለህይወታችን መመሪያ በማድረግ በፀሎት ክፋትን በማሸነፍ የተሻለዉን እና የሚበልጠዉን የእግ/ርን በረከት ለመቀበል እንድንችል መበርታት ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ ቃል የምንረዳዉ ክፋትን በእረሱ በመታመን በማሸነፍ ፍቃዳችንን ለእርሱ በማስገዛት በእምነት ፀንተን ለሌሎች ምስክሮቹ እንድንሆን እንጋበዛለን፡፡እንዲሁም የእግዚአብሔርን መመልከት በእርሱም ፍቃድ መመላለስ ለቅድስና የተጠራንበትን ህይወት እንድንኖር ብርታት ይሆነናል፡፡በመጨረም ቃሉን ለህይወታችን መመሪያ በማድረግ በፀሎት ክፋትን በማሸነፍ የተሻለዉን እና የሚበልጠዉን የእግ/ርን በረከት ለመቀበል እንድንችል መበርታት ያስፈልጋል፡፡

ምንባቡ ስለምን ያናገራል?

ሙሉ እምነት አለን? ሙሉ እምነት እንዲኖረን ምን ማድረግ አለብን ?

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት