እኛ ማነን

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሥር የምንገኝ ሲታውያን መነኮሳን በአገራችን በአዲስ አበባ፣ በመንዲዳ፣ በሆሣዕናና በጎንደር ገዳማት ሲኖሩን፤ ዓላማችንም በወንጌል ላይ የተመሠረተውን የቅዱስ አቡነ ቡሩክ ደንብን (The Rule of St. Benedict) በመከተል ክርሰቲያናዊ የጥምቀት ጸጋችንን በምልአት በሲታዊ ትውፊት መኖር ነው።.....

ይህም በምንኩስና ሕይወታችን፤ በግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ጸሎትና ሥራ በቀጣይነት እግዚአብሔርን የመፈለግና የማመስገን ሕይወት ነው። በአጭር ቃላት ሕይወታችን “ጸሎትና ሥራ” (Ora et Labora) በሚለው ዘመን ጠገብ ትውፊታችን ይገለጻል።

ለዚህም ግብ መሳካት “ከክርስቶስ ፍቅር ምንም ነገር ያለማስበለጥ” የሚለውን ደንባችንን በማሰላሰል ለእግዚአብሔር መንግሥት መስፋትና ምስክርነት በጸጋው ተማምነን ለመኖር የወሰንን ነን።

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እምነት መንፈሳዊ ትምህርቶች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ታሪክ፣ ሥርዓተ አምልኮ፣ ጸሎቶችና መንፈሳዊነትን ወደ ምንካፈልበት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ዜና ወደ ሚነገርበት፣ እንዲሁም በተቀደሰ ጋብቻም ሆነ በምንኩስና ሕይወት ወደ ቅድስና ጥሪ ለመጓዝ የሚያግዙ እውነታዎች ወደሚጋሩበት፣ የቅዱሳን ሕይወት፣ ሀብትና ትሩፋት ወደ ሚነገርበት፣ ባጠቃላይ የአምላካችን መልካም ዜና ወደሚታወጅበት ይህ ድረ ገጽ እንኳን በደህና መጡ!!

ከመ በኲሉ ይሴባሕ እግዚአብሔር!- እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።1ጴጥ.4:11

Map St Joseph Cistercians

Top Panel

ግንቦት 19 ቀን 2004 - እጆቹን አንስቶ ባረካቸው የዕርገት በዓል ይሁንልን

ግንቦት 19 ቀን 2004 - እጆቹን አንስቶ ባረካቸው የዕርገት በዓል ይሁንልን

ሮሜ 1ዐ፡1-13 1ጴጥ 3፡13-22 ሉቃስ 24፡ 45-53

ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ አምስት ኪ.ሜ ርቆ ከደብረዘይት ወዲያ የሚገኝ መንደር የማርያም፣ የማርታና የአልአዛር እንዲሁም የለምጻሙ የስምኦን መኖሪያ የነበረና ከዮርዳኖስ በስተምስራቅ የሚገኝ መንደር ነው ቢታንያ የስሙም ትርጓሜ የበለስ ቤት ማለት ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በኋላ ሐዋርያቱን ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ አግኝቷቸው በመካከላቸው በመሆን ከእነሱ ጋር በሕይወት እያለ በነብያት በሙሴ ሕግና በመዝሙራት ስለእርሱ ይነገር የበረውን እናም እርሱ የነገራቸውን ሁሉ አእምሯቸውን ከፍቶላቸው እንዲያስተውሉ አድርጓቸው ነበር፡፡ ቃሉን የሚያከብር አምላክ ቃሉን ጠብቆ የራሱን ቃል አከበረው ስለራሱ የተነገሩትን ሁሉ ደግሞ ደጋግሞ አደረገው ሰዎች ነንና ያየነውን የሰማነውን ለማመን እንቸገራለን ግን ለምን? ማመን ለምን ይሳነናል? በእርግጥ የእግዚአብሔር ድንቀ ስራዎች ከሰዎች እምነት በላይ ድንቅ ነው፡፡ ስለዚህ ይመስላል ሰዎች አድራጊው አምላክ የሚያደርጋቸው ድንቅ ነገሮች በሰው ልጅ አእምሮ ሊገመት የሚችል ባለመሆኑ ማመን ያዳግተናል ምንም እንኳን የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አምሳያ የተፈጠረ ቢሆንም አእምሮ ግን የሰው ልጅ ይለያል፡፡ ስለዚህ ቀድሞ ሐዋርያቶች በዓይናቸው እንዳዩት ሁሉ ዛሬም እኛ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እያየን ስለሆነ አምነን ስንቀበል በተግባር ስንፈጽመው ጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያቶቹን እጆቹን አንስቶ ባርኳቸው ወደ ሰማይ እንዳረገ ሁሉ እኛንም በመጨረሻው ወቅት ይባርከናል፡፡

• ምንባቡ ስለምን ይናገራል?

• በእምነታችን ምን ያህል ጠንካሮች ነን?

• በእምነታችን ጠንካሮች ለመሆን ምን ማድረግ ይገባናል?

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት - ብሉይና አዲስ ኪዳናት 

አድራሻችን

logo

                 ገዳመ ቅዱስ ዮሴፍ ዘሲታውያን

                    ፖ.ሳ.ቁ. 21902
                 አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
             Phone: +251 (116) 461-435

              Fax +251 (116) 458-988

               contact@ethiocist.org

             https://www.ethiocist.org

 
 

ለድረ ገጻችን የሚሆን ጽሑፍ ካለዎ

1- የኢሜል አድራሻችንን webpageorganizers@gmail.comን ተጠቅመው አሊያም

2- ይህን ሲጫኑ በሚያገኙት CONTACT FORMበሚለው ቅጽ ላይ ጽሑፍዎን ለጥፈው ወይም 

3-facebook አድራሻችን https://www.facebook.com/ethiocist.org በግል መልእከት ይላኩልን

በተጨማሪም የሚያካፍሉት ጠቃሚ የድረገጽ አድራሻ ካለዎ ይላኩልን።   

መልእክት ከር.ሊ.ጳ. ፍራንቼስኮስ

pope"ይቅርታን እና ምሕረትን ማድረግ የሰላማዊ ሕይወት መሠረት ነው"።

“ይቅር ማለት እና ምህረትን ማድረግ የሕይወት ዘይቤያችን ቢሆኑ ኖሮ፥ ስንት ጦርነት፣ ስቃይ እና መከራን እናስቀር ነበር! በግንኙነቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የሚያደርግ ፍቅር ያስፈልጋል። ይኸውም በባል እና ሚስት፤ በወላጆች እና በልጆች መካከል እንዲሁም በአካባቢያችን፣ በማኅበረሰባችን እና በፖለቲካውም ማለት ነው። እንዲሁም ይቅርታን ለማድረግ ጥረት የማናደርግ ከሆነ፥ ይቅር አይባልልንም” ማለታቸው ተገልጿል።

ምንጭ - ቫቲካን ራድዮ አማርኛ ዝግጅት